2010–2019 (እ.አ.አ)
ቁስሎቻቸውን ማሰር
ኦክተውበር 2013


ቁስሎቻቸውን ማሰር

በዚህ ምድራዊ ጉዞያችን ጌታ ከኛ ፍት ያስቀመጠውን ለክህንነት አገልግሎት እራሳችን ማዘግጀት እንዳለብን ፀሎቴ ነው።

ሁላችን ስለ ሌሎች ሀላፍነት ተባርከናል። የእግዚአብሄር ክህነት መሸከም ለእግዝአብሄር ልጆች ዘላለማዊ ህይወት ሀላፍነት አለብን። ይህም እውነት ናው፣ ቆንጆም ነው እናም አንዳንዴ አድካም ነው።

ዛሬ ምሽት ምን ማለት እንድፈለኩ በመረዳት የሚያዳምጡ የኮረም ቡድኖች አሉ። ለአንዳችሁ ይህ ነው የተፈጠረው፣ ለብዙዎቻችሁ ከአንድ በላይ ደርሶባችዋል። ዝርዝሩ ብለያይም ሀሳቡ አንድ ነው።

በደንብ የማታውቁት ሽማግሌ ለእርዳታ ይጠይቃችዋል። ከሚኖርበት ቦታ ሚስቱን እና ህፃን ልጁን ቅርበት ወደለው ሌላ አፓርትመንት መቀየር እንዳለበት ከቅርብ ጊዜ በፍት ተረዳ።

እሱና ባሌበቱ እቃቸውን ለሟጓጓዝ ጓደኛቸውን የጭነት መኪና ጠይቆ ነበር። ጓደኛቸውም መኪና እንድዋሱ አድርገዋል። ወጣቱ አባት ያላቸውን ንብረት ወደ መኪና መጫን ጀመረ፣ ነገር ግን ከጥቂት ደቅቃ በኃላ ወገቡን ጎዳ። መኪና ያዋሰው ጓደኛ ለመርዳት ሥራ ይበዛበታል። ወጣቱ አባት ተስፋ ቢስነት ተሰማው። እናተን የኮረም ቡድን ፕሬዝዳንቱን አሰበ።

ለእርዳታ በጠየቀ ጊዜ ከሰዓት በኃላ ነበር፣ በዛን ቀን የቤተክርስትያን ምሽት ስብሰባ ነበር። ያን ቀን ለቤት ቁሳ ቁስ ሥራ ባሌበትህን ለመርዳት ቃል ገብተህ ነበር። ልጆችህ አንድ ነገር አብራቸው እንድሰራ ጠይቆሀል፣ ነገር ግን አልጀመርክም።

የኮረምህ ቡድንህ አባሎች በተለይም የምትተማመናቸው እንደ አንተው እክል አጋጥማቸው ይሆናል።

ጌታ ለዝህ ሥራ ጥሪ ስያቀርብልህ የዚህ አይነት ቀን እንድምያጋጥምህ ስለምያውቅ የሚያበረታታ ተረት ሰጥቶሀል። ሥራ ለበዛባቸው የክህነት ሥልጣን ያዥዎች ምሳሌ ነው። አንዳንዴ ሳምራዊ ወይም በፍቃዱ ሰውን የሚረዳ ሰው ታሪክ እንላለን። ታሪኩ ግን ሥራ በተበዛበት በኃላኛው ቀን ለክህነት ሥልጣን ያዥዎች ተብሎ ነው።

ሥራ ለበዛበት የክህነት አገልጋይ ታሪኩ ፍፁም የሆነ ነው። እናንቴ ሳምራዊ ሰው እንጅ ቄስ ወይም እንደ ሌቭ የቆሰለውን ሰው አይቶ የሚያልፍ እንዳልሆናችሁ አስታውሱ።

ችግር ስያጋጥማችሁ ይህን ታሪክ ላታስቡ ልሆን ይችላል። ያ ቀን እንደገና ስመጣ እንደምታስቡ ፀሎቴ ነው።

ሳምራዊ ሰው ከኢየሩሳለም ወደ ጄርኮ የተጓዙበት ምክንያት በቅዱስ መፅሀፍ አልተነገረንም። ሌቦች ስለ መንገድ አስጊነት ያልተረዱትን እንደምጠብቁ በማወቅ ዝም ብሎ ለሽርሽር የሄደ አይደለም። እንደተለመደው ለምር ጉዳይ ነበር። የጭነት አህያ እና ወይን ጠጅም ይዞ ነበር።

በጌታ ቃል እንደተነገረው ሳምራዊው የቆሰለውን ሰው ባየ ጊዜ ቆመ ምክንያቱም ርህራሄ ስላለው ነው።

ከርህራሄ ስሜት በላይ አደረገ። ሁል ጊዜ የጉዳዩን ልዩ ዝርዝር አስታውሱ።

“ቀርቦም ዘይትና የወይን ጠጅ በቍስሎቹ ላይ አፍስሶ አሰራቸው፥ በራሱ አህያም ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደርያ ወሰደው ጠበቀውም።

“በማግሥቱም ሁለት ዲናር አውጥቶ ለባለቤቱ ሰጠና። ጠብቀው፥ ከዚህም በላይ የምትከስረውን ሁሉ እኔ ስመለስ እከፍልሃለሁ አለው።”1

እናንቴ የክህነት ሥልጣን ያዥዎች ጥሪያችሁ ሶስት ማረጋገጫዎች አሉት። አንደኛ ርህራሄ ለምያስፈልጋቸው ከጠየቃችሁ ጌታ ይሰጣችዋል። ሁለተኛ ሌሎችን ለአገልግሎት ተሳታፍ እንድሆኑ እንደ ጠባቅ ያዘጋጃል። ሶስተኛ ጌታ እንደ ደግ ሳምራዊ ለተቸገሩት እርዳታ ላደረጉት ሁሉ ሽልማት ያደርጋል።

እናንቴ የኮረም ቡድን ፕሬዝዳንቶች ለዝህ ማረጋገጫ ከአንድ በላይ አድርጋችዋል። ሌሎች የጌታ ክህነትን በርሀራሄ እርዳታ እንድያደርጉ በድፍረት ጠይቃችዋል። ብዙውን ጊዜ መልስ የሚሰጡትን ደጋግማችሁ ለመጠየቅ አልፈራችሁም፣ ምክንያቱም በቀላሉ ርህራሄ እንደምሰማቸው ታውቃላችሁ። ቀደም ስል ለመርዳት ስመርጡ የጌታ ልገሳ እንደተሰማቸው በማወቅ ነው የጠየቃችሁ። ብዙ አስተዋፅዎ ከማድረግ ከጌታ የተሻለ ካስ መግኜት እንደምቻል በማወቅ ከባድ ችግር ያለባቸውን ጠይቃችዋል። ባለፈው እርዳታ ያደርጉት የአዳኝን ምስጋና ከገደብ በላይ ተሰምቶአቸዋል።

ጭነቱን ወደ መኪና መጫን እና ማውረድ አንድን ሰው አለመተየቅ ተስምቶአችሁ ይሆናል። እንደ መሪነታችሁ የቡድናችሁን አባሎች እና ቤተሰባቸውን በደንብ ታውቃላችሁ። ጌታም ሙሉ በሙሉ ያውቃቸውል።

የትኛው ሚስት ችግር እንዳላት ያውቃል፣ ምክንያቱም ባለቤቷ የጠየቀችውን እንድያደርግ ጊዜ የለውምና። አባታቸው እንደገና አንድ ጊዜ ሄዶ ሌሎችን ሰለረዳ በማየት የተባረኩ ልጆች እንዳሉ ያውቃል። ወይም ልጆች አባታቸው ያን ቀን አብረው እንድውሉ ፈልገው ይሆናል። እሱም ግን ለማገልገል ማን ግብዣ እንደምያስፈልገው ያውቃል። ግን በፍቃደኝነት እጩ ላይኖር ይችላል።

እናንቴ የኮረም አባላችሁን ሙሉ በሙሉ አታውቁም። ነገር ግን እግዚአብሄር ያውቃል። ብዙውን ጊዜ እንዳደረጋችሁ ለሌሎች እርዳታ እንድያደርጉ ማንን መጠየቅ እንዳለባችሁ ፀሎት አድርጋችዋል። ጌታ ማን መጠየቅ እና በረከት ማግኘት እንዳለበት እና የትኛው ቤተሰብ ሳይጠየቁ በረከት ማግኘት እንዳለባቸው ያውቃል።

ወጣት በነበርኩ ጊዜ ይህ ስሆን አይቻለሁ። የቄሶች ቡድን ረዳት ነበርኩ። አንድ ቀን ቆጳስ ስልክ ደወለልኝ። ባሏን ያጣች ችግርተኛ ሴት እንድንጠይቅ ፈልጎ ነበር።

መጥቶ እንድወስደኝ በመጠበቅ ላይ እያለሁ ተረበሽኩኝ። ቆጳሱ ጠንካራ ረዳቶች እንዳለው አውቃለሁ። አንደኛው ታዋቅ ዳኛ ነበር። ሌላኛው ትልቅ ኩባንያ የነበረው እና በኃላ የበላይ ባለሥልጣን የሆነ ሰው ነበር። ቆጳስም አንድ ቀን የበላይ ባለሥልታን ሆኖ ልያገለግል ይችላል። ቆጳስ ለምንደነው ልምድ የለሌውን ቀስ “እርዳታህን እፈልጋለሁ የምለው?”

ለእኔ ያለውን አሁን በተሻለ አውቃለሁ። “ጌታ ልባርካችሁ ይፈልጋል።” ቀደም ስል እሱ የተወላትን ፎርም ካልሞላች ከቤተክርስትያን እርዳታ እንደማታገኝ ብሎ ለሴቷ ስናገር አይቻለሁ። ወደ ቤት ስንመለስ ስለተገረምኩኝ በታፈነ ሳቅ “የራሷ ወጪን ስትቆጣጠር ሌሎችን መርዳት ትችላለች” አለ።

በሌላ ወቅትም ቆጳሴ የመጠጥ ሱሰኛ ወላጆች ቤት ውስዶኝ ነበር። እነሱም ፍራቻ ያለባቸው ሁለት ትናንሽ ሴት ልጆችን እኛን ለማናገር ወደ በር ላኩ። ሁለቱን ትናንሽ ሴት ልጆች ከጎበኘን በኃላ ወደ እኔ ዞር በማለት “በህይወታቸው ያለውን አደጋ ገና መለወጥ አንችልም፣ ነገርግን ጌታ እንደምወዳቸው ይሰማቸዋል” አለ።

ሌላ ጊዜ አንድ ምሽት ለአመታት ወደ ቤተክርስትያን ያልመጣው ሰው ቤት ወሰደኝ። ቆጳሱ ምን ያህል እንደምወደው እና ዎርድ ምን ያህል እንደምፈልገው ነገረው። በሰውየው ላይ ለውጥ የታየ አይመስልም። ነገር ግን በዚያን ጊዜ እና ሁል ጊዜ ቆጳስ አብረው ከሱ ጋር ስወስደኛ ታላቅ ተፅእኖ አድርጎብኛል።

በዝህ ጉብኝት የትኛው ቄስ በረከት ማግኘት እንዳለበት ቆጳስ ፀሎት ማድረጉን በምንም መንገድ ማወቅ አልችልም። ብዙውን ጊዜ ሌሎች ቄሶችን አብረው ውስዶ ይሆናል። ነገር ግን ጌታ አንድ ቀን እኔ ቆጳስ በመሆን እምነታቸው የቀዘቀዘውን ወደ ሞቃት ወንጌል እንድመለሱ እንደምጋብዝ ያውቃል። አንድ ቀን በመቶ እና በሺ ለሚቆጠሩ የግዚአብሄ ልጆች ጊዜያዊ ነገር ለምያስፈልጋቸው የክህነት ሥልጣን ሀላፍነት እንደምሰጠኝ ጌታ ያውቃል።

እናንቴ ወጣቶች ጌታ ለየትኛው የክህነት አገልግሎት ሥራ እንደምያዘጋጃችሁ አታውቁም። ነገር ግን ለማንኛውም የክሀነት ሥልጣን ያዥ ታላቅ ፍተና መንፈሳዊ እርዳታን መስጠት ነው። ሁላችንም ያን ሀላፍነት አለን። የቡድኑ አባል ከመሆን ይመጣል። የቤተሰብ አባል ከመሆን ይመጣል። የማንኛውም ቡድናችሁ ወይም ቤተሰባችሁ እምነት በሰይጣን ጥቃት ከደረሰባቸው ሪህራሄ ይሰማችዋል። በሰማራዊው አገልግሎትና ምህረት እንደተሰጠ እናንተም ደግሞ ቁስላቸውን በመታሻ ቅባት ታድናላችሁ።

ለሚስዮን ሥራ አገልግሎት በሺ ወደምቆጠሩ ሰዎች ለመንፈሳዊ ፍለጋ ትሄዳላችሁ። ከማስተማራችሁ በፍት ብዙዎቹ ቁስንል የሚያድን እና ችግርን የሚፈታ መንፈሳዊነት እንዳላችሁ አያውቁም። ለጌታ ሥራ እነሱን ለማዳን ትሄዳላችሁ። ወደ ዘላለማዊ ህይወት የሚመራውን ሥርአቶች የሚቀበሉ ከሆነ ጌታ ብቻ ነው መንፈሳዊ ቁስላቸውን መለወስ የምችለው።

እንደ ቡድን አባላት፣ የቤት አስተማሪነት እና ሚስዮኒነት የራሳችሁ እምነት ንቁ ካልሆነ መንፈሳቸው የተበላሸውን ሰዎች መርዳት አትችሉም። ያም ማለት መፅሀፍ ቅዱስ በየጊዜው ከማንበብና ከመፀለይ የበለጠ ነው። ለጥቅት ጊዜ መፀለይና ቅዱስ መፅሀፍ ገልበጥ አድርጎ መመልከት በቅ ዝግጅት አይደለም። የምትፈልጉት የመራጋገጫ ምክር የመጣው ከትምህርትና ቃል ኪዳን አንቀፅ 84 ነው። “እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ ነገር ግን ዘወትር የህይወትን ቃል በአዕምሮዎቻችሁ ውስጥ አከማቹ፣ እና ይህም በዚያች ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰው ተመዝኖ የሚሰጠው ይሰጣችኋል።”2

ያ በረከት ልጠየቅ የሚገባው ለህይወት ቃሎች በፅናት ዋጋ ከሰጠን ነው። ለቅዱስ መፅሀፍ ዋጋ መስጠት ለኔ ስለቃሉ በስሜት መስማት ማለት ነው። ለምሳሌ ስለ ነቢይ ጆሴፍ ስሚዝ መለኮታዊ ጥሪ በእምነታቸው ወላዋይ የሆኑትን ሰዎች ሄጀ ለመርዳት ስሞክር ስሜቱ ወደ እኔ ይመለሳል።

የመፅሀፈ ሞርሞን ቃል ብቻ አይደለም። ሁለት መሰመር እንኳ ከመፅሀፈ ሞርሞን ሳነብ የሚመጣ የእውነት ማረጋገጫ ስሜት ነው። ስለ ነቢይ ጆሴፍ ስሚዝ በጥርጣሬ ለተበከለ እያንዳንዱ ሰው እንደምመጣ ቃል መግባት አልችልም። ጆሴፍ ስሚዝ የዳግም መመለስ ነቢይ እንደሆነ አውቃለሁ። መፅሀፈ ሞርሞን የግዚአብሄር ቃል መሆኑን አውቃለሁ፣ ምክንያቱም አጥንቻለሁና።

እናንቴም የእውነት ማረጋገጫ ከመንፈስ ማግኜት እንድምትችሉ ከልምድ አውቃለሁ፣ ምክንያቱም ለኔ መቷልና። ጌታ እናንተን እና እኔን በእውነታ ጠላት በቆሰሉት ፍት እኛን ከማስቀመጡ በፍት ያን ማረጋገጫ ልኖረን ይገባል።

ሌላ ማድረግ ያለብን ዝግጅቶች አሉ። ስለ ሌሎች ችግር ርህራሄ አለማሳየት የሰው ልጆች ባህሪይ ነው። አዳኝ ስለ እራሱ ሀጢያት ክፍያ የተናገረበት እና ለሰማይ አባታችን ልጆች ችግርና ስቃይ በራሱ ላይ የወሰደበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው።

የተመረጡ የሰማይ አባት ምድራዊ ክህነት ያዥዎች እንኳ በቀላሉ ርህራሄ አይኖራቸውም። እንደ ሰብአዊ ፍጡርነታችን ዝንባሌ ለኛ ግልፅ የሆነውን ማየት ከማይችል ሰው ጋር ትእግስተኞች አይደለንም። ትእግስት አልባ መሆናችን ወደ ውገዛ ወይም ተቃዋሚነት እንዳይተረጎም ጥንቃቄ ማድረግ አለብን።

እንደ ክህነት ሥልጣን አገልጋይነታችን ጌታን ስንዘጋጅ የሚመራንቅዱስ መፅሀፍ አለ። ጌታ የትኛውም ቦታ ብልከን ለጉዞያችን ስጦታ ያቀፈ ነው። ሳማራዊው ሰው ይህን ስጦታ ነበረው። ያስፈልገናል። እንዴት መፈለግ እንዳለብን ጌታ ነግሮናል።

“ስለዚህም፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ ልግስና ከሌላችሁ ከንቱዎች ናችሁ፣ ልግስና አትወድቅምና። ስለሆነም ከሁሉም በላይ ታላቅ የሆነውን ልግስናን ያዙ፤ ሁሉም ነገሮች ይወድቃሉና ፡—

“ነገር ግን ልግስና ንፁህ የክርስቶስ ፍቅር ነው፤ እናም እስከዘለዓለም ይፀናል፤ እናም በመጨረሻው ቀንም እርሱን የያዘ መልካም ይሆንለታል።

“ስለሆነም የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ በልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ተከታዮች ሁሉ ላይ በሚያፈሰው በዚህ ፍቅር ትሞሉ ዘንድ በኃይል ከልባችሁ ወደ አብ ፀልዩ፤ የእግዚአብሔር ልጆች ትሆኑ ዘንድ፣ እርሱ በሚመጣበትም ጊዜ እንደእርሱ ሆነን እንዳለ እናየዋለንና፣ ይህ ተስፋም ይኖረናልና፣ ልክ እርሱ ፍፁም እንደሆነ እኛም ፍፁማን እንሆናለንና።”3

በምድራዊ ጉዞያችን ለክህነት አገልግሎት ጌታ ከኛ ፍት ለምያስቀምጠው ሁሉ እራሳችን እንድናዘጋጅ ፀሎቴ ነው። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን።