ምዕራፍ ፴
የተለወጡት አህዛብ ከቃል ኪዳን ህዝብ ጋር ይቆጠራሉ—ብዙ ላማናውያንና አይሁዶች በቃሉ ያምናሉ እናም ያማሩ ይሆናሉ—እስራኤል ዳግም ትመለሳለች፣ እናም ኃጢአተኞች ይጠፋሉ። ከ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም አሁን እነሆ፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ እናገራችኋለሁ፤ እኔ ኔፊ እናንተ አህዛቦች ከሚሆኑት የበለጠ ፃድቃን እንሆናለን ብላችሁ እንድታስቡ አልፈቅድም። እነሆም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ካልጠበቃችሁ በተመሳሳዩ ሁላችሁም ትጠፋላችሁ፤ እናም በተነገረው ቃል ምክንያት አህዛብ በሙሉ ጠፍተዋል ብላችሁም አታስቡ።
፪ እነሆም፣ እላችኋለሁ ንሰሃ የሚገቡት አህዛቦች የጌታ ሀቃል ኪዳን ህዝብ ናቸው፤ እናም ንሰሃ የማይገቡት ለአይሁዶችም ይጣላሉ፤ ምክንያቱም ጌታ ሐንስሀ በሚገቡት እና የእስራኤል ቅዱስ በሆነው በልጁ ከሚያምኑት በስተቀር ለማንም ቃል ኪዳን አልገባምና።
፫ እናም አሁን፣ በይበልጥ ስለአይሁዶችና ስለአህዛብ በመጠኑ ትንቢት እናገራለሁ። እኔ የተናገርኳችሁ መፅሐፍ ከመጣ፣ እናም ለአህዛቦች ከተፃፈና፣ በድጋሚ ወደ ጌታ ከታተመ በኋላ፣ በተፃፉት ቃላት ሀየሚያምኑ ብዙዎች ይኖራሉ፤ እና ለእነርሱም ለቀሩት ዘሮቻችን ያደርሱአቸዋል።
፬ እናም ከዚያ በኋላ የእኛ ዘሮች ቅሪት እኛን በተመለከተ፣ እንዴት አድርገን ከኢየሩሳሌም እንደወጣን፣ እናም እንዴትስ እነርሱ የአይሁድ ትውልድ እንደሆኑ ያውቃሉ።
፭ እናም የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ሀበእነርሱ መካከላቸው ይሰበካል፤ ስለሆነ፣ ለእነርሱም ወደ አባቶቻቸው እውቀት፣ እናም ደግሞ በአባቶቻቸው መካከል ወደ ነበረው የኢየሱስ ክርስቶስ ሐእውቀት ይመለሳሉ።
፮ እናም ከዚያ በኋላ ይደሰታሉ፤ ምክንያቱም ይህ ከእግዚአብሔር እጅ የተሰጣቸው በረከት እንደሆነ ያውቃሉ፤ እናም የጨለማው ቅርፊት ከዐይናቸው መውደቅም ይጀምራል፤ እናም ንፁህና ሀአስደሳች ህዝቦች እስኪሆኑ ድረስ ብዙ ትውልድ ከእነርሱ አያልፍም።
፯ እናም እንዲህ ይሆናል የተበተኑት ሀአይሁዶች ደግሞ በክርስቶስ ማመን ለይጀምራሉ፤ በምድር ፊትም ላይ መሰብሰብ ይጀምራሉ፤ እናም በክርስቶስ የሚያምኑ ብዙዎችም አስደሳች ህዝብ ይሆናሉ።
፰ እናም እንዲህ ይሆናል ጌታ እግዚአብሔር በምድር ላይ የህዝቡን ዳግም መመለስ ለማምጣት በሁሉም ሀገሮች፣ ወገኖች፣ ቋንቋና ህዝብ መካከል ስራውን ይጀምራል።
፱ እናም ሀጌታ እግዚአብሔር ድሆችን በፅድቅ ለይፈርዳል፣ የምድር ሐትሁታንም በእኩልነት ይገስጻል። እናም ምድርን በአፉ በትር ይመታል፤ በከንፈሩም ትንፋሽ ኃጢአተኞችን ይገድላል።
፲ ጌታ እግዚአብሔር በሰዎች መካከል ታላቅ ሀክፍፍል የሚያደርግበት ለጊዜ በፍጥነት ይመጣል፣ እናም በደለኞችን ያጠፋል፤ እናም ህዝቡን ሐይምራል፣ አዎን፣ በደለኞችን በእሳት መማጥፋት ቢኖርበትም።
፲፩ እናም ሀፅድቅነትም የወገቡ መታጠቅያው፣ ታማኝነትም የጎኑ መቀነትይሆናል።
፲፪ ሀእናም ተኩላ ከበጉ ጋር ይኖራል፤ አቦሸማኔውም ከፍየል ግልገሎች ጋር፣ ጥጃውም የአንበሳ ደቦልም፣ ከፍሪዳውም ጋር በአንድ ላይ ይተኛሉ፤ እናም ትንሽ ልጅም ይመራቸዋል።
፲፫ እናም ላምና ድብ አብረው ይመገባሉ፤ ግልገሎቻቸውም በአንድነት ይተኛሉ፤ እናም አንበሳም እንደ በሬ ገለባ ይበላል።
፲፬ እናም የሚጠባው ህፃን በመርዛማው እባብ ጉድጓድ ላይ ይጫወታል፣ እናም ጡት የጣለውም ህፃን በእፉኝት ቤት ላይ እጁን ይጭናል።
፲፭ በተቀደሰው ተራራዬ ላይ ሁሉ አይጎዱም፣ አይጠፉምም፤ ውሃ ባህርን እንደሚሸፍን ሁሉ ምድር በጌታ እውቀትም ትሞላለችና።
፲፮ ስለሆነም፣ ሀየሁሉም ሀገሮች ነገሮች ይታወቃሉ፤ አዎን፣ ሁሉም ነገሮች ለሰው ልጆች ለይገለጣሉ።
፲፯ ሀያልተገለጠ፣ ሚስጥር የሆነ ምንም የለም፤ በብርሃን የማይወጣ የጨለማ ስራ የለም፤ እናም የማይፈታ በምድር ላይ የሚታተም ምንም ነገር አይኖርም።
፲፰ ስለሆነም፣ ለሰው ልጆች ተገልጠው የነበሩት ሁሉም ነገሮች በዚያ ቀን ይገለጣሉ፤ እናም ከእንግዲህ ወዲህ ሰይጣን በሰዎች ልጆች ልብ ላይ ሀምንም ስልጣን ለብዙ ጊዜ አይኖረውም። እናም አሁን የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ንግግሬን እፈፅማለሁ።