ምዕራፍ ፬
ሌሂ ዘሮቹን መከረ እንዲሁም ባረከ—ሞተና ተቀበረ—ኔፊ በእግዚአብሔር ቸርነት ተደሰተ—ኔፊ እምነቱን ለዘለዓለም በጌታ አደረገ። ከ፭፻፹፰–፭፻፸ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም አሁን፣ እኔ ኔፊ፣ አባቴ ወደ ግብፅ ተወስዶ ስለነበረው ሀዮሴፍ የተናገራቸውን ትንቢቶች በተመለከተ ተናገርኩ።
፪ እነሆም እርሱ ዘሮቹን በተመለከተ በእውነት ተንብዮአል። እናም እርሱ ከፃፋቸው የበለጡ ሀትንቢቶች ብዙ የሉም። እናም እርሱ እኛን እንዲሁም የወደፊቱን ትውልድ በተመለከተ ተንብዮአል፤ እና እነሱም በነሀስ ሰሌዳው ላይ ተፅፈዋል።
፫ ስለሆነም፣ አባቴ የዮሴፍን ትንቢት በተመለከተ መናገሩን ካቆመ በኋላ፣ የላማንን ወንዶችና ሴቶች ልጆች ጠርቶ እንዲህ አላቸው—እነሆ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቼ ሀየበኩር ልጄ ወንዶች ልጆችና ሴቶች ልጆች የሆናችሁ፣ ቃሌን እንድታደምጡ እፈልጋለሁ።
፬ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ብሏልና—ትዕዛዛቴን እስከጠበቃችሁ ሀድረስ በምድሪቷ ላይ ትበለፅጋላችሁ፤ እናም ትዕዛዛቴን የማትጠብቁ ከሆነ ከፊቴ ትለያላችሁ።
፭ ነገር ግን እነሆ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቼ፣ ለእናንተ ሀበረከትን ሳልተውላችሁ ወደ መቃብሬ መሄድ አልችልም፤ እነሆም መሄድ ባለባችሁ ለመንገድ ካደጋችሁ ከእርሱ እንደማትሸሹ አውቃለሁ።
፮ ስለሆነም፣ ከተረገማችሁ፣ እነሆ፣ እርግማኑ ከእናንተ እንዲወሰድና በወላጆቻችሁ ሀራስ ላይ ይመለስ ዘንድ በረከቴን በእናንተ ላይ እተዋለሁ።
፯ ስለሆነም፣ በእኔ በረከት የተነሳ ጌታ እግዚአብሔር እናንተ እንድትጠፉ ሀአይፈቅድም፤ ስለሆነም፣ እርሱ ለዘለዓለም ለእናንተ እና ለዘሮቻችሁ ለመሀሪ ይሆናል።
፰ እናም እንዲህ ሆነ አባቴ ለላማን ወንዶችና ሴቶች ልጆች መናገሩን ካቆመ በኋላ፣ የልሙኤልን ወንዶችና ሴቶች ልጆች በፊቱ እንዲቀርቡ አስደረገ።
፱ እናም እርሱ እንዲህ ሲል ተናገራቸው—እነሆ፣ የሁለተኛው ወንድ ልጄ ወንድና ሴት ልጆች የሆናችሁ ወንዶችና ሴት ልጆቼ፤ እነሆ እኔ ለላማን ወንዶችና ሴቶች ልጆች የሰጠሁት አይነት በረከት እሰጣችኋለሁ፤ ስለሆነም እናንተ ፈፅሞ አትጠፉም፤ ነገር ግን በመጨረሻ ዘሮቻችሁ ይባረካሉ።
፲ እናም እንዲህ ሆነ አባቴ ለእነርሱ መናገሩን ከጨረሰ በኋላ፣ እነሆ፣ ሀየእስማኤልን ወንዶች ልጆች፣ አዎን፣ እናም ቤተሰቡን ሁሉ ተናገራቸው።
፲፩ እናም እርሱ እነርሱን መናገር ካቆመ በኋላ፣ ለሳም እንዲህ ሲል ተናገረው፥ አንተ የተባረክህ ነህ፣ እንዲሁም ዘርህ፤ ምክንያቱም እንደወንድምህ ኔፊ ምድሪቱን ትወርሳለህና። እናም ዘርህ ከእርሱ ዘር ጋር ይቆጠራል፤ እናም አንተ ልክ እንደ ወንድምህ ትሆናለህ፣ ዘርህም ልክ እንደእርሱ ዘር ይሆናል፤ አንተም በዘመንህ ሁሉ ትባረካለህ።
፲፪ እናም እንዲህ ሆነ አባቴ፣ ሌሂ፣ በውስጡ ባለው የልቡ ስሜትና የጌታ መንፈስ መሰረት ለቤተሰቡ ሁሉ ከተናገረ በኋላ አረጀ። እንዲህም ሆነ እርሱም ሞተ፣ እናም ተቀበረ።
፲፫ እናም እንዲህ ሆነ ከሞተ በኋላ ብዙም ቀን ሳይሆን ላማንና ልሙኤል እንዲሁም የእስማኤል ወንድ ልጆች በጌታ ተግሳፅ የተነሳ በእኔ ተቆጡ።
፲፬ እኔ ኔፊ፣ እንደቃሉ እነርሱን እንድናገራቸው ተገፋፍቼ ነበርና፤ እኔ፣ እና ደግሞም አባቴ ከመሞቱ በፊት፣ ብዙ ነገሮችን ተናግረናቸው ነበር፤ ብዙዎቹ አባባሎች ሀበሌሎች ሰሌዳዎቼ ላይ ተፅፈዋል፤ ታሪካዊ የሆነውም ይበልጡ ክፍል በሌላኛው ሰሌዳዎቼ ላይ ተፅፏልና።
፲፭ እናም ሀበእነዚህ ላይ የነፍሴን ነገሮች፣ እናም በነሀስ ሰሌዳዎቹ ላይ የተቀረፁ ብዙዎቹ ቅዱሳት መጻሕፍት እፅፋለሁ። ነፍሴ በቅዱሳት መጻሕፍት ትደሰታለች፣ እንዲሁም ልቤ ለታሰላስላቸዋለች፣ እንዲሁም እኔ እነርሱን ለልጆቼ ሐትምህርትና ጥቅም እፅፋለሁ።
፲፮ እነሆ፣ ሀነፍሴ በጌታ ነገሮች ትደሰታለች፤ እናም ለልቤ ያየኋቸውንና የሰማኋቸውን ነገሮች ላይ ያለማቋረጥ ታሰላስላለች።
፲፯ ይሁን እንጂ፣ ጌታ ታላቅና ድንቅ ስራውን ለእኔ ለማሳየት ምንም እንኳን ሀቸርነቱ ታላቅ ቢሆንም ልቤ ይጮሀል—አቤቱ እኔ ምንኛ ለጎስቋላ ሰው ነኝ! አዎን፣ ልቤ በስጋዬም የተነሳ ያዝናል፤ ነፍሴም በክፋቴ የተነሳ ታዝናለች።
፲፰ እኔ በቀላሉ ሀበሚያስቸግሩኝ መከራዎችና ኃጢአቶች ተከብቤአለሁ።
፲፱ እናም ደስታን በምፈልግበት ጊዜ በኃጢአቴ የተነሳ ልቤ ያዝናል፤ ይሁን እንጂ በማን እንዳመንኩኝ አውቃለሁ።
፳ እግዚአብሔር ረዳቴ ነበር፤ በምድረበዳ ውስጥ በስቃዬ መራኝ፤ እናም በታላቁን ጥልቅ ውኃ ላይ ጠበቀኝ።
፳፩ ሰውነቴን ሁሉ፣ ስጋዬም እስከሚነድ ድረስ፣ ሀበፍቅሩ ሞላኝ።
፳፪ ሀጠላቶቼን በፊቴ በፍርሀት እስኪንቀጠቀጡ ድል ነሳቸው።
፳፫ እነሆ፣ በቀን ጩኸቴን ሰምቷል፣ እናም በምሽት ሀበራዕይ እውቀትን ሰጥቶኛል።
፳፬ እናም፣ በቀን በፊቱ በታላቅ ሀፀሎት ተዳፈርኩ፤ አዎን፣ ድምጼንም ወደላይ ላኩኝ፤ እናም መላዕክት ወርደው አገለገሉኝ።
፳፭ እናም በመንፈሱ ክንፎች ሰውነቴ እጅግ ከፍ ወዳለው ተራራ ሀተወሰደ። እናም ዓይኖቼም ታላቅ ነገሮችን ተመልክተዋል፣ አዎን፣ እንዲያውም ለሰዎች እጅግ ታላቅ የሆነውን፤ ስለዚህ እኔ እነርሱን እንዳልፅፍ ታዝዤ ነበር።
፳፮ አቤቱ አሁን ታላቅ ነገሮችን ካየሁ፣ ጌታ ለሰው ልጆች እራሱን ዝቅ በማድረግ በእንዲህ ዓይነት ምህረቱ ከጎበኛቸው፣ ሀለምንድነው ልቤ የሚያለቅሰው፣ እንዲሁም ነፍሴ በሀዘን ሸለቆ ውስጥ የምትዘገየው፣ እናም ሰውነቴ የሚቃወሰው፣ እናም ጥንካሬዬ በመከራዬ የሚደክመው?
፳፯ እናም ለምን በስጋዬ የተነሳ ለኃጢያት ሀተገዢ እሆናለሁ? አዎን፣ ለምን ለበመከራ ውስጥ እወድቃለሁ፣ ክፉው ሐሰላሜን እንዲያጠፋ እንዲሁም ነፍሴን እንዲያሰቃያት በልቤ ውስጥ ቦታ ያገኛል ዘንድ ለምን በፈተና ተገዢ እሆናለሁ? በጠላቴ የተነሳ ለምን እቆጣለሁ?
፳፰ ነፍሴ ሆይ፣ ንቂ! ከእንግዲህ በኃጢያት አትድከሚ። አቤቱ ልቤ ተደሰቺ፣ እናም ለነፍሴ ሀጠላት ለሆነው ቦታ አትስጪ።
፳፱ በጠላቶቼ የተነሳ በድጋሚ አትቆጪ። በመከራዬም የተነሳ ብርታቴን አታድክሚ።
፴ አቤቱ ልቤ ተደሰቺ፣ እንዲህም በማለት ወደ ጌታ ጩሂ—አቤቱ ጌታ አንተን ለዘለዓለም አወድስሀለሁ፤ አዎን አምላኬና የደህንነቴ ሀአለት ነፍሴ በአንተ ደስ ይላታል።
፴፩ አቤቱ ጌታ፣ ነፍሴን ታድናለህን? ከጠላቶቼስ እጅ ታወጣኛለህን? ሀኃጢያትን በምመለከትበት ወቅት በጥላቻ ታንቀጠቅጠኛለህን?
፴፪ የሲኦል ደጆች ከፊቴ ይዘጉ፣ ምክንያቱም ሀልቤ የተሰበረ እና መንፈሴ የተዋረደ ነውና! አቤቱ ጌታ፣ እባክህ በጥልቁ ሸለቆ ጎዳና ለእጓዝበት ዘንድ በቀናው መንገድ እፀና ዘንድ፣ የፅድቅን በሮች ከፊቴ አትዝጋ!
፴፫ አቤቱ ጌታ፣ እባክህ የፅድቅህን መጎናፀፊያ ደርብልኝ! አቤቱ ጌታ፣ እባክህ ከጠላቶቼ የምሸሽበትን መንገድ አዘጋጅልኝ! እባክህ መንገዴን አቅናልኝ! እባክህ በመንገዴ እንቅፋትን አታድርግ—ነገር ግን አንተ መንገዴን ታጠራልኛለህ፣ እናም የጠላቶቼን መንገድ እንጂ የእኔን አትዘጋብኝም።
፴፬ አቤቱ ጌታ፣ በአንተ ታምኛለሁ፣ እንዲሁም ለዘለዓለም በአንተ ሀእታመናለሁ። ለእምነቴን በስጋ ክንድ ላይ አላደርግም፤ ምክንያቱም በስጋ ክንድ ላይ ሐየሚታመን የተረገመ እንደሚሆን አውቃለሁና። አዎን፣ በሰው ላይ እምነት የሚያደርግ ወይም ስጋ ለባሹን ክንዱ የሚያደርግም ሰው የተረገመ ነው።
፴፭ አዎን፣ እግዚአብሔርን ሳይነቅፍ ለለመነ ለእርሱ ሀበልግስና እንደሚሰጠው አውቃለሁ። አዎን፣ አምላኬን ለየተሳሳተ ነገር ሐካልጠየቅሁት በስተቀር ይሰጠኛል፤ ስለዚህ ወደ አንተ ድምፄን ከፍ አደርጋለሁ፤ አዎን፣ አምላኬ የፅድቄ አለት ወደሆንከው አንተም እጮሀለሁ። እነሆ፣ መአለቴና የዘለአለም አምላኬ፣ ድምፄ ለዘለዓለም ወደ አንተ ከፍ ይላል። አሜን።