ምዕራፍ ፯
ያዕቆብ ከኢሳይያስ ማንበቡን ቀጠለ፥ ኢሳይያስ እንደ መሲሁ ይናገራል—መሲሁ የተማሩ ሰዎች ልሳን ይኖረዋል—ለሚገርፉት ጀርባውን ይሰጣል—እርሱ አያፍርም—ኢሳይያስ ፶ን አነጻፅሩ። ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ አዎን፣ ጌታ እንዲህ ይላል—ፈትቻችኋለሁን፣ ወይንስ ለዘለዓለም ወርውሬአችኋለሁ? ጌታ እንዲህ ይላል—እናታችሁን የፈታሁበት የፍቺዋ ፅህፈት የት አለ? ለማን ነው አሳልፌ የሰጠኋችሁ? ወይስ እናንተን ሀየሸጥኩት ከአበዳሪዎች ለየትኛው ነው? አዎን፣ ለማን ሸጥኳችሁ? እነሆ፣ ስለኃጢአታችሁ ራሳችሁን ሸጣችኋል፣ እናም ስለመተላለፋችሁ እናታችሁም ተፈታለች።
፪ ስለሆነም፣ እኔ ስመጣ ማንም ሰው አልነበረም፤ ሀበምጣራበትም ጊዜ አዎን፣ የሚመልስ አልነበረም። የእስራኤል ቤት ሆይ፣ መታደግ እንዳትችል እጄ ፈፅሞ አጥራለች፣ ወይስ ለማዳን ኃይል የለኝምን? እነሆ በግሰጻዬ ለባህሩን አደርቃለሁ፣ ሐወንዞችንም ምድረበዳ አደርጋለሁ እናም መአሳዎቻቸው ውሃው በመድረቁ ይገማሉ፣ እናም በጥማት ይሞታሉ።
፫ ሰማያትን ሀጥቁረት አለብሳቸዋለሁ፣ እናም መሸፈኛቸውን ለማቅ አደርጋለሁ።
፬ የእስራኤል ቤት ሆይ ጌታ እግዚአብሔር በትክክለኛው ጊዜ ለእናንተ እንዴት መናገር እንድችል የተማሩትን ሀልሳን ሰጥቶኛል። እናንተ በደከማችሁ ጊዜ ማለዳ በማለዳ ያነቃችኋል። እንደተማሪ እንድሰማ ጆሮዬን ያነቃቃል።
፭ ጌታ እግዚአብሔር ሀጆሮዬን ከፍቷል፣ እናም እኔ አመፀኛ አልነበርኩም፣ ወደኋላም አልተመለስኩም።
፮ ጀርባዬን ሀለገራፊዎች፣ እናም ጉንጬንም ለፀጉር ነጪዎች ሰጠሁ። ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስኩም።
፯ ጌታ እግዚአብሔር ይረዳኛል፣ ስለዚህም አላፍርም። ስለዚህ ፊቴን እንደባልጩት ድንጋይ አድርጌዋለሁ፣ እናም እንደማላፍር አውቃለሁ።
፰ እናም ጌታ ቅርቤ ነው፣ እርሱም ያጸድቀኛል። ከእኔ ጋር የሚከራከር ማነው? በአንድነት እንቁም። ጠላቴስ ማነው? ወደ እኔ እንዲቀርብ ፍቀዱለት እናም በአፌ ኃይለ ቃል እመታዋለሁ።
፱ ጌታ እግዚአብሔር ይረዳኛል። እናም እኔን ሀየሚኮንኑ ሁሉ፣ እነሆ፣ ሁሉ እንደ ልብስ ያረጃሉ፣ እናም ብል ይበላቸዋል።
፲ ከእናንተ መካከል ጌታን የሚፈራ፣ የአገልጋዩን ሀድምፅ የሚታዘዝ፣ በጨለማ የሚራመድ እንዲሁም ብርሃን የሌለው ማነው?
፲፩ እነሆ እናንተ እሳት የምታነዱ ሁሉ፣ የእሳትንም ወላፈን የምትጭሩ፣ ሀበእሳታችሁ ብርሃን እና ባነደዳችሁት ወላፈን ተመላለሱ። ይህ ከእጄ ይሆንባችኋል—በሀዘንም ትሞታላችሁ።