ክፍል ፻፲፪
በሀምሌ ፳፫፣ ፲፰፻፴፯ (እ.አ.አ.) በከርትላንድ ኦሀዮ ውስጥ ስለአስራ ሁለቱ የጥቦው ሐዋሪያት በሚመለከት ለቶማስ ቢ ማርሽ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል የተሰጠ ራዕይ። ይህን ራዕይ የተቀበለው ሽማግሌዎች ሂበር ሲ ኪምባል እና ኦርሰን ሀይድ በእንግሊዝ ሀገር ወንጌሉን ለመጀመሪያ ጊዜ በሰበኩበት ቀን ነው። ቶማስ ቢ ማርሽ በዚህ ጊዜ የአስራ ሁለቱ ሐዋርያት ቡድን ፕሬዘደንት ነበር።
፩–፲፣ አስራ ሁለቱ ወንጌሉን ይላኩ እና ለሁሉም ሀገሮች እና ህዝብም የማስጠንቀቂያን ድምፅ ያንሱ፤ ፲፩–፲፭፣ መስቀላቸውን ይሸከሙ፣ ኢየሱስንም ይከተሉ፣ እና በጎቹንም ይመግቡ፤ ፲፮–፳፣ የቀዳሚ አመራርን የሚቀበሉ ጌታን ይቀበላሉ፤ ፳፩–፳፱፣ ጭለማ ምድርን ሸፈነ፣ እና የሚያምኑ እና የሚጠመቁ ብቻ ይድናሉ፤ ፴–፴፬፣ ቀዳሚ አመራር እና አስራ ሁለቱ የዘመን ፍጻሜ ሙላትን ቁልፎች ይዘዋል።
፩ ለአገልጋዬ ቶምስ በእውነት ጌታ እንዲህ ይላል፥ ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ እና በስሜ እንዲመሰክሩ እና በሁሉም ሀገር፣ ነገድ፣ ቋንቋና ህዝብ መካከል ወደ ውጪ ሀእንዲላኩ በተመረጡት፣ እና በአገልጋዮቼ መሳሪያነት በተሾሙት በእነዚያ ወንድሞችህ ወኪል ያቀረብከው ምፅዋትህ እንደ ለማስታወሻ ወደ እኔ ዘንድ መጥቷል።
፪ እውነት እልሀለሁ፣ እኔ ጌታ በልብህ ውስጥ እና ከአንተም ጋር ያልተደሰትኩባቸው አንዳንድ ጥቂት ነገሮች አሉኝ።
፫ ይህም ቢሆን፣ ራስህን ሀእስካዋረድህ ድረስ ከፍ ትደረጋለህ፤ ስለዚህ ኃጢአቶችህ ሁሉ ተሰርየዋል።
፬ ልብህ በፊቴ ሀሀሴትን ያድርግ፤ እና ለለአህዛብ ብቻ ሳይሆን ደግሞም ሐለአይሁዶች ስለስሜ ትመሰክራለህ፤ እና ቃሌን ወደ ምድር ዳርቻዎች ትልካለህ።
፭ ሀአትጣላ፣ ስለዚህ ጠዋት በየማለዳው፣ በየቀኑ ለየማስጠንቀቂያህ ድምፅህ ይሂድ፤ እና ሲመሽም፣ በንግግርህ ምክንያት የምድር ነዋሪዎች ያንቀላፉም ዘንድ አትፍቀድ።
፮ በፅዮን ውስጥም መኖሪያህ ይታወቅ፣ እና መኖሪያህንም ሀአትቀይር፤ በሰዎች ልጆች መካከል ስሜን ታሳውቅ ዘንድ፣ እኔ ጌታ ታከናውነው ዘንድለአንተ ታላቅ ስራ አለኝና።
፯ ስለዚህ ለስራውም ወገብህን ሀአጥብቅ። እግሮችህም ይጫሙ፣ አንተ የተመረጥህ ነህና፣ እና መንገድህም በተራራዎች መካከል እና ከብዙ ህዝብ መካከል ነውና።
፰ እና በቃልህም ከፍ ያሉት ሀየዋረዱ ይሆናሉ፣ እና በቃልህም የተዋረዱት ከፍ ይላሉ።
፱ ድምፅህም ለሚተላለፈው ግሳጼ ይሆናል፤ እና በግሳጼህም ስምን የሚያጠፋ ምላስም ጠማማነቱን ያቁም።
፲ ሀትሁት ሁን፤ እና ጌታ አምላክህ እጅህን ይዞ ይመራሀል፣ እና ለጸሎቶችህም መልስ ይሰጥሀል።
፲፩ ልብህን አውቃለሁ፣ እና ስለወንድሞችህም ጸሎትህን ሰምቻለሁ። ለእነርሱ ከሌሎች በላይ ሀበፍቅርህ አድሎን አታድርግ፣ ነገር ግን ለእነርሱ ያለህ ፍቅርህ እንደራስህ ይሁን፤ እናም ፍቅርህም ለሁሉም ሰዎችና ስሜን ለሚወዱ ሁሉ ይብዛ።
፲፪ ለአስራ ሑለቱ ወንድሞችህም ጸልይ። ስለስሜም ብለህ በብርቱ ገስጻቸው፣ እና ለኃጢአቶቻቸው ሁሉ ይገሰጹ፣ እና ሀስለስሜም በፊቴ ታማኝ ሁን።
፲፫ ሀከፈተናዎቻቸው እና ከብዙም ለስቃይ በኋላ፣ እነሆ፣ እኔ ጌታ እፈልጋቸዋለሁ፣ እና ልባቸውን ባያጠጥሩ፣ እና አንገታቸውን በእኔ ላይ ባያደነደኑ፣ ሐይለወጣሉ፣ እኔም እፈውሳቸዋለሁ።
፲፬ አሁን፣ እልሀለሁ፣ እና ለአንተ የምለውን፣ ለአስራ ሁለቱ ሁሉ እላለሁ፥ ተነሳ እና ወገብህን አጥብቅ፣ ሀመስቀልህንም ተሸከም፣ ተከተለኝ፣ እና በጎቼንም ለመግብ።
፲፭ ራሳችሁን ከፍ አታድርጉ፤ በአገልጋዬ ጆሴፍ ላይ ሀአታምጽ፤ በእውነት እልሀለሁ፣ ከእርሱ ጋር ነኝ፣ እና እጄም በእርሱ ላይ ይሆናልና፤ እና እኔ ለእርሱ፣ እና ዳግሞም ለእናንተም፣ የሰጠኋቸው ለቁልፎችም እስከምመጣ ድረስ ከእርሱ አይወሰዱም።
፲፮ እውነት እልሀለሁ አገልጋዬ ቶማስ፣ በሀገሮች ሁሉ መካከል በውጪ ስላሉት አስራ ሁለቱን በሚመለከት፣ የመንግስቴን ቁልፎች እንድትይዝ የመረጥኩህ ሰው ነህ—
፲፯ አገልጋዬ ጆሴፍ፣ እና አገልጋዬ ሀስድኒ፣ እና አገልጋዬ ለሀይረም ሊመጡበት በማይችሉበት ስፍራ ሁሉ የመንግስትን በር እንድትከፍት ዘንድ፤
፲፰ በእነርሱም ላይ ለጥቂት ዘመን የቤተክርስቲያናትን ሽክሞች ሁሉ በእነርሱ ላይ አሳርፌአለሁና።
፲፱ ስለዚህ፣ የትም ቢልኩህ፣ ሂድ፣ እና እኔም ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ እና ስሜን በምታውጅበት በማንኛውም ስፍራ ቃሌን ይቀበሉ ዘንድ ሀውጤታማ በርም ይከፈትልሀል።
፳ ማንም ቃሌን ሀየሚቀበል እኔን ይቀበላል፣ እና እኔን የሚቀበል ማንም፣ የላኳቸውን፣ ስለስሜም ለአንተ አማካሪዎች ያደረኳቸውን እነዚያን የቀዳሚ አመራርን ይቀበላል።
፳፩ ደግሞም፣ እውነት እላችኋለሁ፣ በስሜ፣ በወንድሞቻችሁ ሀበአስራ ሁለቱ ድምፅ፣ በእናንተ ተገቢ ትእዛዝና ለስልጣን፣ የምትልኳቸው ሁሉ፣ በምትልኳቸው በየትኛውም ሀገር የመንግስቴን በር የመክፈት ሀይል ይኖራቸዋል—
፳፪ ይህን የሚሆነው በፊቴ ራሳቸውን ትሁት እስካደረጉ፣ እና በቃሌም እስከኖሩ፣ እና የመንፈሴንም ድምፅ ሀእስካደመጡ ድረስ ነው።
፳፫ እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ሀጭለማ ምድርን፣ እና ታላቅ ጭለማም የህዝብን አዕምሮ ሸፍኗል፣ እና ስጋ ለባሽ ሁሉ በፊቴ ለበስብሰዋል።
፳፬ እነሆ፣ ሀበቀል፣ የቁጣ ቀን፣ የንዳድ ቀን፣ የጥፋት ቀን፣ ለየለቅሶ ቀን፣ የሀዘን ቀን በምድር ነዋሪዎች ላይ በፍጥነት መጥቷል፤ እና እንደ አውሎ ንፋስም በምድር ፊት ሁሉ ይመጣል፣ ይላል ጌታ።
፳፭ እና በቤቴም ላይ ሀይጀምራል፣ እና ከቤቴም ይሄዳል፣ ይላል ጌታ፣
፳፮ መጀመሪያ ስሜን እናውቃለን ሀበሚሉ ለበማያውቁኝም፣ እና በቤቴም መካከል እኔን ሐስለሰደቡኝ ስለእነዚያ በመካከላችሁ ስላሉት፣ ይላል ጌታ።
፳፯ ስለዚህ፣ በዚህ ስፍራ ስላለው የቤተክርስቲያኔ ጉዳዮች እንዳታስቡበት ይሁን፣ ይላል ጌታ።
፳፰ ነገር ግን በፊቴ ልባችሁን ሀአንጹ፤ ከዚያም ወደ አለም ሁሉ ለሂዱ፣ እና ላልተቀበሉት ለእያንዳንዱ ፍጥረትም ወንጌሌን ስበኩ፤
፳፱ እና ሀያመነ እና ለየተጠመቀም ይድናል፣ እና ያላመነ፣ እና ያልተጠመቀ ሐይፈረድበታል።
፴ ለእናንተ ሀለአስራ ሁለቱና ለአማካሪዎቻችሁ እና መሪዎቻችሁ እንዲሆኑም ለተመደቡት ለእነዚያ ለለቀዳሚ አመራር የዚህ ክህነት ሀይል የሙሉ ሐዘመን ፍጻሜ ለሆነው ለመጨረሻዎቹ ቀናት እና ለመጨረሻ ጊዜም ተሰጥቷል፣
፴፩ ሀይልን የምትይዙት፣ ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ በማንኛውም ዘመን ከተቀበሉት ሁሉ ጋር በተገናኘ ነው፤
፴፪ እውነት እላችኋለሁ፣ የተቀበላችሁት የዘመን ሀቁልፎች ከአባቶች ለየመጡ እና በመጨረሻም ወደ እናንት ከሰማይ የተላኩ ናቸውና።
፴፫ እውነት እላችኋለሁ፣ ጥሪአችሁ እንዴት ታላቅ እንደሆነ ተመልከቱ። የዚህ ትውልድ ደም ከእጆቻችሁ ሀእንዳይጠየቁ፣ ልባችሁንና ልብሶቻችሁን ለአንጹ።
፴፬ እስከምመጣም ድረስ ታማኝ ሁኑ፣ ቶሎ ሀእመጣለሁና፤ እና ለእያንዳንዱም ሰው እንደ ለስራው እንዲከፈለው ደመወዙም ከእኔ ዘንድ ነው። እኔ አልፋ እና ኦሜጋ ነኝ። አሜን።