ክፍል ፻፴፩
በግንቦት ፲፮ እና ፲፯፣ ፲፰፻፵፫ (እ.አ.አ.) በራመስ ኢለኖይ ውስጥ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የተሰጡ መመሪያዎች።
፩–፬፣ የሰለስቲያል ጋብቻ ከፍ ባለው ሰማይ ዘለአለማዊ ክብር ለማግኘት አስፈላጊ ነው፤ ፭–፮፣ ሰዎች ለዘለአለም ህይወት እንዴት እንደታተሙ ተገልጿል፤ ፯–፰፣ መንፈስ ሁሉ ግዝፈት ያለው ነው።
፩ ሀበሰለስቲያል ክብር ውስጥ ሶስት ሰማያት ወይም ደረጃዎች አሉ፤
፪ ሀከፍተኛውን ለማግኘት፣ ሰው ወደ እዚህ የክህነት ስርዓት መግባት አለበት [ይህም ለአዲስ እና ዘለአለማዊ የጋብቻ ቃል ኪዳን ማለት ነው]፤
፫ እና ይህን ባያደርግ፣ ሊያገኘው አይችልም።
፬ ወደሌሎቹ ለመግባት ይችላል፣ ነገር ግን ያም የሚያደርገው መጨረሻው መንግስቱ ነው፤ ሀተጨማሪም ሊያገኝ አይችልም።
፭ [ግንቦት ፲፯፣ ፲፰፻፵፫ (እ.አ.አ.)]። በተጨማሪ እርግጠኛ ሀየትንቢት ቃል ማለት በራዕይ እና በትንቢት መንፈስ፣ በቅዱስ የክህነት ሀይል አማካይነት፣ ሰው ለለዘለአለም ህይወት ሐእንደታተመ አውቋል ማለት ነው።
፯ ስለዚህ፣ ህልውና የሌለው ህልው ነገር የሚባል ነገር የለም። ሀመንፈስ ሁሉ ህልውና ያለው ነው፣ ነገር ግን ይህም የጠራ እና ንጹህ ነው፣ እና ሰውም ሊለየው የሚችለው ለበነጹ አይኖች ብቻ ነው፤
፰ እናየውም ዘንድ አይቻለንም፤ ነገር ግን ሰውነቶቻችን ሲነጹ ግዝፈት ያለው እንደሆነ ሁሉ እናያለን።