ክፍል ፷፭
ጥቅምት ፴፣ ፲፰፻፴፩ (እ.አ.አ.)፣ በሀይረም ኦሀዮ፣ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል ስለጸሎት የተሰጠ ራዕይ።
፩–፪፣ የእግዚአብሔር የመንግስቱ ቁልፎች በምድር ለሰው ተሰጥተዋል፣ እናም ወንጌሉም አሸናፊ ይሆናል፤ ፫–፮፣ የአንድ ሺህ ዘመን መንግስተ ሰማያት ይመጣል እናም በምድርም በእግዚአብሔር መንግስት ጋር ተዋሀዳለች።
፩ አድምጡ፣ እናም ሀያል እና ጠንካራ የሆነው፣ አካሄዱም እስከ ምድር ዳርቻ የሆነውን፣ አዎን ድምጹም ለሰዎች የሆነውን፣ ከላይም እንደተላከ ድምጽ የሆነውን፣ እነሆ—የጌታን መንገድ ሀአዘጋጁ፣ ጥርጊያውንም አቅኑ፤
፪ በምድርም ለሰው የእግዚአብሔር ሀመንግስት ለቁልፎችም ተሰጥተዋል፣ እናም ከዚህም ወንጌሉ፣ እጅም ሳይነካው ከተራራው ተፈንቅሎ ምድርን ሐእስከሚሞላ ድረስ እንደሚንከባለለውም መድንጋይ፣ ወደ ምድር ዳርቻምይገፋል።
፫ አዎን፣ ድምፅም ይጮሀል—የጌታን መንገድ አዘጋጁ፣ የበጉን ሀእራት አዘጋጁ፣ ለለሙሽራውም ተዘጋጁ።
፬ ወደ ጌታም ጸልዩ፣ ቅዱስ ስሙንም ጥሩ፣ በአህዛብም መካከል ድንቅ ስራዎቹን እንዲታወቁ አድርጉ።
፭ የዚህች ኗሪዎችም እንዲቀበሉት፣ መንግስቱም በምድር ላይ እንዲሄድ፣ ጌታን ጥሩ፣ እናም የሰው ልጅ ሀየክብሩን ብርሀን ለለብሶ ከሰማይ በምድር ከተሰራችው የእግዚአብሔርን ሐመንግስት ጋር ለመገኛኘት መበሚገለጥበት ወደ ፊት ለሚመጡት ቀናትም ተዘጋጁ።
፮ ስለዚህ፣ ሀመንግስተ ሰማያት እንድትመጣ፣ የእግዚአብሔር ለመንግስት ወደ ፊት ይሂድ፣ አንተም፣ እግዚአብሔር ሆይ፣ በሰማይም እንዳከበርህ እንዲሁ በምድርም ትከበር ዘንድ፣ ጠላቶችህም ይዋረዱ ዘንድ፤ ክብርም፣ ኃይልም፣ እና ግርማም ሐየአንተ ናትና፣ ከዘለአለም እስከዘለዓለም። አሜን።