ኑ፣ ተከተሉኝ 2024 (እ.አ.አ)
[ሚያዝያ 15–21 ፡ “እንደፈቃዱ ለማድረግ በእኔ ይሰራል” ኢኖስ–የሞርሞን ቃላት


“ሚያዝያ 15–21 (እ.አ.አ)፡ “እንደፈቃዱ ለማድረግ በእኔ ይሰራል” ኢኖስ–የሞርሞን ቃላት፣ ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ መፅሐፈ ሞርሞን 2024 (እ.አ.አ) [2024 (እ.አ.አ)]

“ሚያዝያ 15–21 (እ.አ.አ)። ኢኖስ–የሞርሞን ቃላት፣ ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ መፅሐፈ ሞርሞን 2024 (እ.አ.አ) [2024 (እ.አ.አ)]

ምስል
ኢኖስ በልጅነቱ ከአባቱ ከያዕቆብ እና ከእናቱ ጋር

ያዕቆብ እና ኢኖስ በስኮት ስኖው

ሚያዝያ 15—21፡ “እንደፈቃዱ ለማድረግ በእኔ ይሰራል”

ኢኖስ–የሞርሞን ቃላት

ኢኖስ የሥጋ ረሃብን ለማርካት አውሬ ለማደን ወደ ጫካ ቢሄድም “ነፍሱ ስለ ተራበች” ቀኑን ውሎ ለሊቱን እዚያው አሳለፈ። ይህ ረሃብ ኢኖስ ድምፁ “ወደ ሰማይ እስከሚደርስ” ከፍ እንዲል አድርጎታል። ይህንን ልምድ በእግዚአብሔር ፊት እንደ ትግል ገልጿል (ሄኖስ 1፡2–4 ይመልከቱ)። ከኢኖስ እንደምንማረው ከሆነ፣ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ እና ፈቃዱን ለማወቅ ከልብ የሚደረግ ጥረት ነው። በዚህ ሐሳብ ስትጸልዩ፣ ልክ እንደ ኢኖስ፣ እግዚአብሔር እንደሚሰማችሁ እና ስለ እናንተ፣ ስለምትወዷቸው ሰዎች እንዲሁም ለጠላቶቻችሁም እንደሚያስብ ልታውቁ ትችላላችሁ (ኢኖስ 1፡4–17 ይመልከቱ)። ፈቃዱን ስታውቁ፣ ይበልጥ ፈቃዱን መፈጸም ትችላላችሁ። እንደ ሞርሞን እናንተም “ሁሉንም ነገሮች [አታውቁም] ነገር ግን፤ … ; እንደ ፈቃዱ ለማድረግ [በእናንተ] ውስጥ ይሰራል” ((የሞርሞን ቃላት 1፡7).

በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር የሚረዱ ሃሳቦች

ኢኖስ 1፡1-17

እግዚአብሔር ጸሎቴን አድምጦ ይመልስልኛል።

ከጸሎት ጋር ያላችሁ ተሞክሮ እንደ ኢኖስ ድራማዊ ላይሆኑ ይችላሉ፣ ነገር ግን ትርጉም የሌላቸው አይደሉም። ኢኖስ 1፡1–17ን ስታጠኑ ልታስቡባቸው የሚገቡ አንዳንድ ጥያቄዎች እዚህ አሉ።

  • ኢኖስ ሲጸልይ ያደረገውን ጥረት የሚገልጹት የትኞቹ ቃላት ናቸው?

  • የኢኖስ ጸሎት ከቁጥር 4 ወደ 11 እንዴት ተቀየረ?

  • ጸሎቴን ለማሻሻል የሚረዳኝን ከኢኖስ ምን ተማርኩ?

በተጨማሪም “ኢኖስ በኃይል ይጸልያል [Enos Prays Mightily]” (ቪዲዮ)፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት፣ “ጣፋጭ የጸሎት ሰዓትመዝሙሮች፣ ቁ. 142ን ይመልከቱ።

የውይይት ጥያቄዎችን ማጋራት። ሌሎችን የምታስተምሩ ከሆነ፣ ሁሉም ሰው እንዲያያቸው መወያየት የምትፈልጓቸውን ጥያቄዎች በአንድ ግልጽ ቦታ ላይ አድርጉ። ይህ ሰዎች ጥያቄዎቹን እንዲያስቡ እና የበለጠ ተነሳሽነት ያላቸው መልሶችን እንዲሰጡ ይረዳል።

ምስል
የሴሚነሪ መለያ

ኢኖስ 1፥1-4

ጌታ በቤተሰቤ መልካም ተጽዕኖ እንድፈጥር ሊረዳኝ ይችላል።

ምናልባት በቤተሰባችሁ ውስጥ ወደ ክርስቶስ እንዲመጣ ለመርዳት የምትፈልጉት ሰው ኖሮ ጥረታችሁ ለውጥ ያመጣ እንደሆን ታስቡ ይሆናል። ያዕቆብ በልጁ በኢኖስ ላይ ስላሳደረው ተጽዕኖ ከኢኖስ 1፡1-4 ምን መማር ትችላላችሁ? ለምሳሌ “በጌታ አስተዳደግና ተግሳጽ” የሚለው ሐረግ ለእናንተ ምን ትርጉም አለው? በቤታችሁ ውስጥ የእርሱን ተጽእኖ እንዴት መጋበዝ ትችላላችሁ?

ስለ ቤተሰባችሁ ስታስቡ፣ እነዚህን ጥያቄዎች እና መርጃዎች አስቡባቸው፡-

ሽማግሌ ዲዬተር ኤፍ. ኡክዶርፍ ለቤተሰቦች ጠቃሚ ምክርን በ“በሚያድኑ ምስጋና [Praise of Those Who Save]” (ኢንዛይን ወይም ሊያሆና፣ ግንቦት 2016 (እ.አ.አ)፣ 77–80) አጋርተዋል። ቤተሰባችሁን ለማጠናከር የእሱ መልእክት ምን እንድታደርጉ አነሳሳችሁ? (በተለይ “ቤተሰቦቻችንን ማዳን [Saving Our Families]” የሚለውን ክፍል ይመልከቱ)።

በተጨማሪም የወንጌል አርእስቶችን፣ “ቤተሰብን፣” የወንጌል ቤተ መጻሕፍትን፤ “ቤትና ቤተሰብ—በትንንሽ ነገሮች [Home and Family—Through Small Things]” (ቪዲዮ)፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት ላይ ይመልከቱ።

ኢኖስ 1፥1-18

በክርስቶስ በማመን ምህረትን ማግኘት እችላለሁ።

አንዳንድ ጊዜ ንስሐ ከገባችሁም በኋላ ኃጢያቶቻችሁ ይቅር ተብለው እንደሆን ልታስቡ ትችላላችሁ። በኢኖስ 1፡1-8 ካለው የኢኖስ ልምድ ምን ግንዛቤዎችን አገኛችሁ? ኢኖስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርታ ከማግኘቱ በፊት እና በኋላ ያለውን እምነት ያሳየው እንዴት ነው?

ጃሮም–ኦምኒ

ትእዛዛቱን ለመጠበቅ ስጥር፣ እግዚአብሔር ይባርከኛል።

የጃሮም እና የኦምኒ መጻሕፍት፣ በጽድቅ እና በብልጽግና መካከል ያለውን ግንኙነት ይገልጻሉ። ከጃሮም 1፡7–12ኦምኒ 1:5–7, 12–18 ምን ትማራላችሁ? አለማዊ የብልጽግና ትርጉሞች ከጌታ ፍቺ የሚለዩት እንዴት ነው? ጌታ ህዝቡ እንዲበለጽግ የሚረዳው እንዴት ነው? (አልማ 37፡1348፡15–16 ይመልከቱ)።

ኦምኒ 1:25–26

“የእስራኤል ቅዱስ ወደሆነው ወደ ክርስቶስ እንድትመጡ”

“ወደ ክርስቶስ እንድትመጡ” የሚለው ግብዣ ብዙ ጊዜ በመጽሐፈ ሞርሞን ውስጥ ይታያል። እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ከመጽሐፉ ዋና ዓላማዎች መካከል አንዱ ይህንን ግብዣ ለሁሉም ሰው ማድረስ ነው። ኦምኒ 1፡25–26 ን ስታነቡ፣ ወደ ክርስቶስ እንዴት እንደሚመጣ የሚገልጹ ምን ቃላት ወይም ሀረጎችን ታገኛላችሁ? ፈጽማችሁ ወደ እርሱ እንድትመጡ ምን ታደርጋላችሁ?

ምስል
ሞርሞን ወርቃማውን ሰሌዳዎች በማጠናቀር ላይ

ሞርሞን ሰሌዳዎችን እያጠናቀረ በጆርጅ ኮኮ

የሞርሞን ቃላት 1፥1-8

ምሪቱን ስከተል እግዚአብሔር በእኔ በኩል ይሰራል።

ጌታ በመፅሐፈ ሞርሞን ውስጥ የኔፊን ትንንሽ ሰሌዳዎች ሞርሞን እንዲያካትት ያነሳሳበት አንዱ ምክንያት እግዚአብሔር የመጀመሪያዎቹ 116 የተተረጎሙ ገፆች እንደሚጠፉ ስለሚያውቅ ነው (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 10ቅዱሳንጥራዝ 1፣ ምዕራፍ 5 ይመልከቱ)። ሞርሞን እነዚህን ጽሑፎች (ከ1 ኔፊ እስከ ኦምኒ) ለማካተት የጌታን መመሪያ በመከተሉ ለምን አመስጋኝ ናችሁ? ሞርሞን እነሱን ለማካተቱ ምን ምክንያቶችን ሰጠ? (የሞርሞን ቃላት 1፡3–7 ይመልከቱ)። እግዚአብሔር በእናንተ ወይም በሌሎች ሲሰራ ያያችሁት መቼ ነው?

ተጨማሪ ሀሳቦችን ለማግኘት፣ የዚህን ወር የሊያሆና እና ለወጣቶች ጥንካሬ መጽሔቶችን እትሞችን ይመልከቱ።

ልጆችን ማስተማርያ ሀሳቦች

ኢኖስ 1፥1-5

የሰማይ አባትን በጸሎት አማካኝነት ማነጋገር እችላለሁ።

  • ልጆቻችሁ ጸሎታቸውን ይበልጥ ትርጉም ያለው እንዲያደርጉ መርዳት የምትችሉት እንዴት ነው? ኢኖስ ሲጸልይ የሚያሳይ ምስል አሳይታችሁ ያዩትን እንዲገልጹ አድርጓቸው። ከዚያም ዓይኖቻቸውን ጨፍነው ከሰማይ አባት ጋር ፊት ለፊት እየተነጋገሩ እንደሆነ ማሰብ ይችላሉ። ስለ ምን ማውራት ይፈልጋሉ? እርሱስ ምን ሊላቸው ይፈልግ ይሆናል?

  • ኢኖስ 1፡1–5ን ጮክ ብላችሁ ስታነቡ፣ ትናንሽ ልጆች እያደኑ፣ ለመጸለይ እየተንበረከኩ እና የመሳሰሉትን በማድረግ ኢኖስን እንደሆኑ ማስመሰል ይችላሉ። ትልልቅ ልጆች የኢኖስን ጸሎት የሚገልጽ ቃል ወይም ሐረግ ማዳመጥ ይችላሉ። እነዚህ ቃላት ስለ ኢኖስ ጸሎት ምን ይነግሩናል? “[ነፍሳችሁ የተራበችበትን]” እና “[ወደ ጌታ የጮሃችሁበትን]” (ኢኖስ 1፡4) ተሞክሮ አካፍሉ።

ምስል
ቤተሰብ እየጸለየ

እንደ እግዚአብሔር ልጆች፣ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንችላለን።

ኢኖስ 1፥2-16

የሰማይ አባት ጸሎቴን አድምጦ ይመልሳል።

  • የሰማይ አባት ጸሎታቸውን እንደሚሰማ እና እንደሚመልስ ልጆቻችሁ እንዲረዱ እንዴት መርዳት ትችላላችሁ? በተለምዶ የሚጸልዩባቸው አንዳንድ ነገሮችን እንዲዘረዝሩ ለመጋበዝ አስቡ። ከዚያም ኢኖስ በኢኖስ 1፡2፣ 9፣ 13–14 እና 16 ላይ የጸለየውን እንዲያገኙ መርዳት ትችላላችሁ (በተጨማሪም“ምዕራፍ 11፡ ኢኖስ፣” መጽሐፈ ሞርሞን ታሪኮች፣ 30–31 ይመልከቱ)።

    የኢኖስ ጸሎት ውጤቱ ምን ነበር? (ቁጥር 6፣9፣ 11 ይመልከቱ)።

    ጸሎታችንን እንዴት ማሻሻል እንዳለብን ከኢኖስ ተሞክሮ ምን እንማራለን?

  • እንደ “የሕፃን ጸሎት” (የልጆች መዝሙር መጽሐፍ፣ 12–13) አይነት ስለ ጸሎት አንድ መዝሙር ዘምሩ። ምናልባት ልጆቻችሁ “ጸልዩ” ወይም “ጸሎት” ወይም ሌሎች የተደጋገሙ ቃላትን በሰሙ ቁጥር እጃቸውን ማንሳት ይችሉ ይሆናል። የሰማይ አባት ጸሎቶቻችሁን የመለሰባቸውን አንዳንድ መንገዶች ለልጆቻችሁ ንገሩ።

የሞርሞን ቃላት 1፡3–8

መንፈስ ቅዱስን ሳዳምጥ ሌሎችን መባረክ እችላለሁ።

  • ሞርሞን በመፅሐፈ ሞርሞን ውስጥ የኔፊን ትናንሽ ሰሌዳዎች ለማካተት የመንፈስ ቅዱስን ምሪት ተከትሏል። በዚህ አመት በመፅሐፈ ሞርሞን የተማርናቸው ነገሮች ሁሉ ወደ እኛ የመጡት ሞርሞን መንፈስን ለማድመጥ በመምረጡ ምክንያት ነው። ልጆቻችሁ መንፈስን ስለ ማዳመጥ እንዲማሩ እንዴት መርዳት ትችላላችሁ? በየሞርሞን ቃላቶች 1፡3–8 ያሉትን ጥቅሶች በየተራ እንዲያነቡ ጋብዟቸው። ከእያንዳንዱ ጥቅስ ስለሚማሩት ነገር መናገር ትችላላችሁ። ከዚያም ልጆቻችሁ የሚከተሉትን ማድረግ ይችላሉ:

    • በዚህ ዓመት በመፅሐፈ ሞርሞን ውስጥ ካሉ ታሪኮች የተማሩትን ማካፈል (በኑ፣ ተከተሉኝ ላይ ያሉ ምስሎች እንዲያስታውሱ ይረዷቸዋል)።

    • እንደ “The Still Small Voice” (የልጆች የመዝሙር መጽሐፍ፣ 106–7) አይነት ስለ መንፈስ ቅዱስ የተዘመረ መዝሙር አብራችሁ ዘምሩ።

    • ሌላ ሰውን የሚባርክ ነገር እንድታደርጉ በመንፈስ የተመራችሁበትን ገጠመኞችን ተናገሩ።

ተጨማሪ ሀሳቦችን ለማግኘት፣ የዚህን ወር የጓደኛ መጽሔት እትም ይመልከቱ።

ምስል
ኢኖስ ሲጸልይ

ሄኖስ እየጸለየ፣ በሮበርት ቲ ባሬት