ኑ፣ ተከተሉኝ 2024 (እ.አ.አ)
ግንቦት 13–19 : “ሊጨልም የማይችል ብርሃን” ሞዛያ 11–17


“ግንቦት 13–19 : “ሊጨልም የማይችል ብርሃን” ሞዛያ 11-17፤ “ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ መፅሐፈ ሞርሞን 2024 (እ.አ.አ) [2024 (እ.አ.አ)]

“ግንቦት 13–19 ሞዛያ 11-17፤ “ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ መፅሐፈ ሞርሞን 2024 (እ.አ.አ) [2024 (እ.አ.አ)]

ምስል
አቢናዲ ለንጉሥ ኖህ ሲመሰክር

አቢናዲ በንጉሥ ኖህ ፊት፣ በአንድሪው ቦስሊ

ግንቦት 13–19 : “ሊጨልም የማይችል ብርሃን”

ሞዛያ 11–17

ትላልቅ እሳቶች ከአንድ ብልጭታ ሊነሱ ይችላሉ። አቢናዲ ለኃያል ንጉሥ እና በቤተ መንግሥቱ ላይ የሚመሰክር አንድ ሰው ነበር። ንግግሩ በአብዛኛው ተቀባይነት አላገኘም፤ ሞትም ተፈረደበት። ሆኖም “ሊጨልም የማይችል ብርሃን” (ሞዛያ 16፡9)፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት፣ በወጣቱ ካህን አልማ ውስጥ የሆነ ነገር አነሳሳ። እናም አልማ ሌሎች ብዙ ሰዎችን ወደ ንስሃ እና በኢየሱስ ክርስቶስ ወደማመን ሲያመጣ የመለወጡ ብልጭታ ቀስ በቀስ እያደገ መጣ። አቢናዲን የገደለው ነበልባል በመጨረሻ ጠፋ፣ ነገር ግን ቃላቱ የፈጠሩት የእምነት እሳት በኔፋውያን እንዲሁም ዛሬ በሚያነቡ ሰዎች ላይ ዘላቂ ተጽእኖ ይኖራቸዋል። አብዛኞቻችን አቢናዲ በምስክርነቱ ምክንያት የደረሰበት ፈጽሞ አይገጥመንም ነገር ግን ሁላችንም ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል የድፍረታችን እና የእምነት ፈተና የሚሆንባቸው ጊዜያት አሉን። ምናልባት የአቢናዲን ምስክርነት ማጥናት በልባችሁ ውስጥ የምሥክርነት እና የድፍረት ነበልባል ሊያነሳሳ ይችላል።

በተጨማሪም “አቢናዲ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመሰክራል ፟፟[Abinadi Testifies of Jesus Christ]” (ቪዲዮ)፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት ላይ ይመልከቱ።

በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር ሀሳቦች

ምስል
የሴሚነሪ ምልክት

ሞዛያ 11–13፣ 17

ብቻዬን ብሆንም ለኢየሱስ ክርስቶስ መቆም እችላለሁ።

ሞዛያ 11–1317ን በምታጠኑበት ጊዜ በዚህ ዝርዝር ውስጥ የአቢናዲን ምስሎች ተመልከቱ። ስለ ክርስቶስ ምስክር ሆኖ ስለመቆም ምን ተማራችሁ? በተለይም ጥናታችሁን በሚከተሉት ምንባቦች እና ጥያቄዎች ላይ ማተኮር ትችላላችሁ፡-

  • ኖህን እና ህዝቡን እንዴት ትገልጻላችሁ? አቢናዲ የእግዚአብሄርን መልእክት ለእነሱ ለማካፈል ድፍረት ያስፈለገው ለምንድን ነው? (ሞዛያ 11:1–19፣ 27–2912:9–15 ይመልከቱ)።

  • አቢናዲን እንዴት መግለፅ ትችላላችሁ? አቢናዲ በምስክርነቱ እንዲደፍር የረዳውን ምን ተገነዘበ? (ሞዛያ 13፡2–9፣ 28፣ 33–3517፡8–10፣ 20 ይመልከቱ)።

ለአዳኙ እና ለወንጌሉ ጥብቅና ብቻችሁን እንደቆማችሁ የተሰማችሁ መቼ ነው? እሱ ከእናንተ ጋር እንደሆነ እንዲሰማችሁ የረዳችሁ እንዴት ነው? ይህንን ስታሰላስሉ፣ በ2 ነገሥት 6፡14–17 ያለውን የኤልሳዕን እና የወጣት አገልጋዩን ታሪክ ማንበብ ትችላላችሁ። ስለዚህ ታሪክ ምን ያነሳሳችኋል?

እንዲሁም ለወጣቶች ጥንካሬ፡ ምርጫ ለመምረጥ መመሪያገጽ 31–33 እውነትን ለመከላከል ድፍረት የሚሰጡ ሀረጎችን ለማግኘት ማሰስ ትችላላችሁ። ወይም እንደ “ትክክለኛውን አድርግ” ወይም “ሁላችንም እንቀጥል” (መዝሙሮች፣ ቁ. 237፣ 243) ባሉ የመዝሙር ግጥሞች ውስጥም እንዲሁ ማድረግ ትችላላችሁ።

ከአቢናዲ የተማራችሁትን እንዴት ተግባራዊ ታደርጋላችሁ? “ለብቻ ለመቆም ድፍረት” (የወንጌል ቤተ መጻሕፍት) የተሰኘው ቪዲዮ ለክርስቶስና ለወንጌሉ መቆም የምትችሉባቸውን ሁኔታዎች ያሳያል። ሌሎች ምን ምሳሌዎችን ማሰብ ትችላላችሁ?

በተጨማሪም ሮሜ 1፡162 ጢሞቴዎስ 1፡7–8፤ “ምዕራፍ 8፡ የድፍረት ጥሪ፣” የቤተክርስቲያኑ ፕሬዘዳንቶች ትምህርቶች፡ ቶማስ ኤስ. ሞንሰን (2022 (እ.አ.አ))፣ 135–47፤ የወንጌል አርእስቶች፣ “በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያለ እምነት፣” የወንጌል ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ይመልከቱ።

በመንፈስ አስተምሩ። “ኃይለኛ የወንጌል ትምህርት፣ ትምህርትን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ስታስተምሩ የመንፈስን መመሪያ ለመስማት እና ለመከተል ራሳችሁን ማዘጋጀትን ይጠይቃል” (በአዳኙ መንገድ ማስተማር፣ 17)።

ሞዛያ 12፡19–37

የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት መፈለግ እና መምረጥ አለብኝ።

የንጉሥ ኖህ ካህናት የእግዚአብሔርን ቃል ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። የቅዱሳት መጻህፍት ጥቅሶችን መጥቀስ እና ትእዛዛቱን እንደሚያስተምሩ ሊናገሩ ይችላሉ። ሆኖም ግን ሕይወታቸው በአዳኙ ወንጌል ያልተነካ ይመስላል። ለምን ነበር?

ሞዛያ 12፡19–37ን ስታነቡ ይህን አስቡ። የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት መፈለግ እና መምረጥ ማለት ምን ማለት ነው ብላችሁ ታስባላችሁ? ወንጌልን በምትማሩበት መንገድ ላይ ለውጦችን እንድታደርጉ የሚያነሳሷችሁ ቃላት ወይም ሀረጎች የትኞቹ ናቸው?

ሞዛያ 13፡11–26

የእግዚአብሔር ትእዛዝ በልቤ ውስጥ መጻፍ አለበት።

ትእዛዛቱ በካህናቱ “[ልብ] ውስጥ አልተጻፉምና” (ሞዛያ 13፡11) የሚለውን የአቢናዲ ምልከታ አሰላስሉ። ይህ ሐረግ ምን ማለት ይሆን? ሞዛያ 13፡11–26ን ስታነቡ፣ እነዚህ ትእዛዛት በልባችሁ ውስጥ ተጽፈው እንደሆን አስቡ።

በተጨማሪም ኤርምያስ 31፡31–34 2 ቆሮንቶስ 3፡3ን ይመልከቱ።

ሞዛያ 14–15

ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኔ መከራን ተቀብሏል።

ሞዛያ 14–15፣ አዳኙን እና ለእናንተ ምን እንደተሰቃየ የሚገልጹ ቃላትን እና ሀረጎች አስተውሉ። ለእርሱ ያላችሁን ፍቅር እና ምስጋና ለመጨመር የሚረዱ ጥቅሶች የትኞቹ ናቸው?

ሞዛያ 15፡1–12

ኢየሱስ ክርስቶስ አብ እና ወልድ የሆነው እንዴት ነው?

አቢናዲ እግዚአብሔር ወልድ—ኢየሱስ ክርስቶስ— አዳኝ እንደሚሆን (ሞዛያ 15፡1 ይመልከቱ)፣ ሰው እና አምላክ በመሆን በስጋ እንደሚኖር አስተምሯል (ቁጥር 2–3)። ለእግዚአብሔር አብ ፈቃድ ራሱን ሙሉ በሙሉ አስገዛ (ቁጥር 5-9)። በዚህ ምክንያት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እና ፍጹም የሆነ የእግዚአብሔር አብ ምድራዊ ምሳሌ ነው (ዮሐንስ 14፡6–10 ይመልከቱ)።

ኢየሱስ ክርስቶስ አብም ነው፣ ቤዛነቱን ስንቀበል፣ “ዘሩ” እና “የእግዚአብሔር መንግስት ወራሾች” እንሆናለን (ሞዛያ 15፡11–12)። በሌላ አነጋገር፣ በእርሱ በመንፈስ ዳግም እንወለዳለን (ሞዛያ 5፡7 ይመልከቱ)።

ስለ ሰማይ አባት እና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚህን እውነቶች ማወቅ አስፈላጊ እንደሆነ የሚሰማችሁ ለምን ይመስላችኋል? የአቢናዲ ምስክርነት በእነሱ ላይ ያላችሁን እምነት የሚያጠናክረው እንዴት ነው?

ልጆችን ለማስተማር የሚረዱ ሀሳቦች

ሞዛያ 11–13፣ 17

ብቻዬን ብሆንም ለኢየሱስ ክርስቶስ መቆም እችላለሁ።

  • አንዳንድ ጊዜ በሕይወታችን ውስጥ ሁላችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ካለን እምነት ጋር የሚቃረኑ ምርጫዎችን እንድናደርግ ጫና ይደርስብናል። በብዙዎች ባይወደድም አቢናዲ የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር ሆኖ ስለመቆሙ ልጆቻችሁ ምን ይማራሉ? በዚህ ዝርዝር ውስጥ ያለው የጥበብ ስራ ወይም “ምዕራፍ 14፡ አቢናዲ እና ንጉስ ኖህ” (በየመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች፣ 38–42) በሞዛያ 11–13 17 ያለውን ታሪክ በምናባቸው እንዲመለከቱ ይረዳቸዋል። ስለ አቢናዲ ምን እንደሚወዱ ጠይቋቸው።

  • ልጆቻችሁ የአቢናዲን ታሪክ ክፍሎች በመተወን ሊደሰቱ ይችላሉ። ከዚያም ሌሎች እነሱ ስህተት እንዲሠሩ ሲፈልጉ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለመለማመድ በእውነተኛ ህይወት ውስጥ ያሉ ሁኔታዎችን ሊያሳዩ ይችላሉ። ወይም ኢየሱስ ክርስቶስን በመከተል ደፋር የሆኑበትን ልምዳቸውን ማካፈል ይችላሉ። አቢናዲ ኢየሱስ ክርስቶስን የተከተለው እንዴት ነው? ( ሞዛያ 13:2–917:7–10 ይመልከቱ)። ንጉሥ ኖኅ ትክክል እንደሆነ የሚያውቀውን ነገር ለምን አላደረገም? ( ሞዛያ 17፡11–12 ይመልከቱ)።

ሞዛያ 12:33–3613:11–24

አሥርቱን ትእዛዛት መጠበቅ አለብኝ።

  • የንጉሥ ኖህ ካህናት ትእዛዛቱን ያውቁ ነበር። ነገር ግን “[በልባቸው እንዲጻፉ]” አላደረጉም (ሞዛያ 13፡11)። ልጆቻችሁ ትእዛዛቱን እንዲያውቁ እና እንዲወዷቸው የምትረዷቸው እንዴት ነው? ምናልባት በሞዛያ12፡33–36 እና 13፡11–24 ያሉትን ትእዛዛት የልብ ቅርጽ ባለው ወረቀት ላይ ይጽፉ ይሆናል። ሲያደርጉት፣ እነዚህ ትእዛዛት ምን ማለት እንደሆኑ እና እንዴት መከተል እንደሚችሉ ከእነሱ ጋር ተነጋገሩ። እነዚህን ትእዛዛት በልባችን እንዴት እንጽፋለን?

  • እንደ “ትእዛዛትን ጠብቁ” (የልጆች የመዝሙር መጽሐፍ፣ 146–47) አይነት ስለ ትእዛዛት መዝሙር አብራችሁ መዘመር ትችላላችሁ። ትእዛዛትን በመጠበቅ ምን በረከቶች ይመጣሉ?

ምስል
አባትና ልጅ ቅዱሳት መጻሕፍትን እያነበቡ

ቅዱሳት መጻሕፍት የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ያስተምሩናል።

ሞዛያ 2፧1716፧4–9

የሰማይ አባት ወደ እርሱ እንዲመልሰኝ ኢየሱስ ክርስቶስን ላከ።

  • ምንም እንኳን አጭር ምዕራፍ ቢሆንም፣ ሞዛያ 14 ኢየሱስ ክርስቶስን የሚገልጹ በርካታ ቃላት እና ሀረጎች አሉት። ምናልባት እናንተ እና ልጆቻችሁ ምዕራፉን አብራችሁ ስታነቡ ልትዘረዝሯቸው ትችላላችሁ። እነዚህን ቃላት እና ሀረጎች ስታጠኑ ስለ አዳኙ ምን እንደሚሰማችሁ ማውራት ትችላላችሁ።

  • አቢናዲ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማስተማር እኛን ከጠፉ በጎች ጋር ያነጻጸረውን ነቢዩ ኢሳይያስን ጠቅሷል። ምናልባት ልጆቻችሁ የሆነ ነገር የጠፋባቸውን ወይም ራሳቸው የጠፉበትን ጊዜ ልምድ ሊያጋሩ ይችላሉ። ምን ተሰማቸው? ምንስ አደረጉ? ከዚያም በአንድነት ሞዛያ 14፡6 እና 16፡4–9ን ማንበብ ትችላላችሁ። ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሚቅበዘበዙ በጎች የሆንነው እንዴት ነው? ኢየሱስ ክርስቶስ እንድንመለስ የሚረዳን እንዴት ነው?

ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር ጓደኛ መጽሔት እትም ይመልከቱ።

ምስል
አቢናዲ ለንጉሥ ኖህ ሲመሰክር

ፊቱ አንጸባረቀ በጄረሚ ዊንቦርግ