መመሪያ መጻህፍቶች እና ጥሪዎች
28.ለሞቱ የሚደረጉ የቤተመቅደስ ሥርዓቶች


“28. ለሞቱ የሚደረጉ የቤተመቅደስ ሥርዓቶች፣” ከአጠቃላይ መመሪያ መፅሐፍ የተመረጡ [2023 (እ.አ.አ)]።

“28. ለሞቱ የሚደረጉ የቤተመቅደስ ሥርዓቶች፣” ከአጠቃላይ መመሪያ መፅሐፍ የተመረጡ

ምስል
ማጥመቂያ ገንዳ

28.

ለሞቱ የሚደረጉ የቤተመቅደስ ሥርዓቶች

28.0

መግቢያ

በቤተመቅደሶች ውስጥ የሚከናወኑ ሥርዓቶች፣ ቤተሰቦች ለዘለዓለም አብረው እንዲሆኑና በእግዚአብሔር ፊት የደስታን ሙላት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።

የሰማይ አባት ልጆች ወደእርሱ ይመለሱ ዘንድ እያንዳንዱ ንስሃ መግባት፣ የደህንነት እና በዘለአለማዊ ህይወት ከፍ ከፍ የማድረግ ሥርዓቶችን ለመቀበል ብቁ መሆን እንዲሁም ከእያንዳንዱ ሥርዓት ጋር ተያያዥ የሆኑትን ቃል ኪዳኖች ማክበር አለባቸው።

የሰማይ አባት፣ ብዙዎቹ ልጆቹ በሥጋዊ ህይወታቸው እያሉ እነዚህን ሥርዓቶች እንደማይቀበሉ ያውቅ ነበር። ሥርዓቶችን የሚቀበሉበትን እና ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን የሚገቡበትን ሌላ መንገድ አቅርቧል። በቤተመቅደስ ውስጥ ሥርዓቶች በውክልና ሊከናወኑ ይችላሉ። ይህ ማለት በህይወት ያለው ሰው ለሞተው ስው በውክልና ሥርዓቶችን ይቀበልለታል ማለት ነው። በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ፣ የሞቱ ሰዎች ለእነርሱ በውክልና የተደረጉላቸውን ሥርዓቶች ለመቀበል ወይም ላለመቀበል መምረጥ ይችላሉ (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 138፥19፣ 32–34፣ 58–59ን ይመልከቱ)።

የቤተክርስቲያኗ አባላት የደህንነትን እና በዘለአለማዊ ህይወት ከፍ ከፍ የመደረግን ሥርዓቶች ያልተቀበሉ በሞት የተለዩ ዘመዶችን እንዲለዩ ይበረታታሉ። ከዚያም አባላት ለእነዚያ ዘመዶች የውክልና ሥርዓቶችን ይፈጽማሉ።

አባላት የቤተሰብ ስሞችን ለቤተመቅደስ ስራ ያላዘጋጁ ከሆነ (28.1.1 ን ይመልከቱ)፣ ሥርዓት የሚያስፈልጋቸው የሞቱ ሰዎች ስም ለቤተመቅደስ ይሰጣል።

28.1

የውክል ሥርዓቶች አጠቃላይ መመሪያዎች

በሞቱበት ጊዜ ዕድሜያቸው 8 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ የነበሩ ሟቾች በእነሱ ምትክ የውክልና ሥርዓቶች ሊደረግላቸው ይችላል። በ28.3 ውስጥ ከተገለጸው በስተቀር፣ ከሚከተሉት ውስጥ አንዳቸው የሚሟሉ ከሆነ ከሞቱ 30 ቀናት እንዳለፋቸው ለሁሉም ሟቾች የውክልና ሥርዓቶች ሊደረጉ ይችላሉ

  • የሟቹ የቅርብ ዘመድ (ያልተፋታ የትደር ጓደኛ፣ ጎልማሳ ልጅ፣ ወላጅ ወይም ወንድም እና እህት) ስሙን ለቤተመቅደስ ሥርዓት ያቀርባሉ።

  • ሥርዓቶችን ለመፈጸም ፈቃድ የሚሰጠው በሟቹ የቅርብ ዘመድ ነው (ያልተፋታ የትደር ጓደኛ፣ ጎልማሳ ልጅ፣ ወላጅ ወይም ወንድም እና እህት)።

ከላይ ከተጠቀሱት ሁኔታዎች አንዳቸውም የማይሟሉ ከሆነ፣ የቤተመቅደስ የውክልና ሥርዓቶች የሚከናወኑት ሟቹ ሰው ከተወለደ ከ110 ዓመታት በኋላ ነው።

28.1.1

የሞቱ ሰዎችን ስሞች ለቤተመቅደስ ሥርዓቶች ማዘጋጀት

የሚቻል ከሆነ የሞቱ የቤተሰብ አባላትን የሚለይ መረጃ FamilySearch.org የቤተመቅደስ ሥርዓቶች ከመከናወናቸው በፊት መግባት አለበት (25.4.2 ይመልከቱ)።

28.1.1.1

የቤተሰብ አባላትን ስሞች ማስገባት

ለውክልና የቤተመቅደስ ሥርዓቶች ስሞችን በሚሰጡበት ጊዜ፣ በአጠቃላይ አባላት የሚዛመዷቸውን ሰዎች ስም ብቻ መስጠት አለባቸው።

28.1.2

ለሞቱ ሰዎች በሚደረጉ የቤተመቅደስ ሥርዓቶች ላይ ማን ሊሳተፍ ይችላል

የታደሰ የቤተመቅደስ መግቢያ መታወቂያ ፈቃድ ያላቸው ሁሉም አባላት ለሞቱ በሚደረጉ የውክልና ጥምቀት እና ማረጋገጫ መቀበል ላይ ላይ መሳተፍ ይችላሉ። የቤተመቅደስ ቡራኬ የተቀበሉ አባላት ለሞቱ በሚደረጉ በሁሉም የቤተመቅደስ ሥርዓቶች ላይ መሳተፍ ይችላሉ። 26.3 ን ይመልከቱ።

28.1.4

መርሃ ግብር ማውጣት

አባላት ለሞቱ ሥርዓቶችን ከማከናወናቸው በፊት ቀጠሮ መያዝ ያስፈልጋቸው ይሆናል። ይመልከቱ temples.ChurchofJesusChrist.org ለእያንዳንዱ የቤተመቅደስ አድራሻ መረጃ እና የጊዜ ሰሌዳ መስፈርቶች።

28.2

ለሞቱ ሰዎች የቤተመቅደስ ሥርዓቶችን ማከናወን

አንድ አባል የውክልና ሥርዓቶችን በሚያከናውንበት ጊዜ፣ ከአባሉ ጋር ተመሳሳይ የውልደት ጾታ ላለው ሟች ሰው ብቻ ወኪል ሆኖ ሊያገለግል ይችላል።

28.2.1

ለሞቱ ሰዎች መጠመቅ እና ማረጋገጫ መቀበል

የታደሰ የቤተመቅደስ መግቢያ መታወቂያ ያለው ማንኛውም አባል በጥምቀት የስራ ምደባ እንዲያገለግል ሊጋበዝ ይችላል። አንዳንድ የሥራ ምደባዎች የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፦

  • በጥምቀቶች እና በማረጋገጫዎች በወኪልነት መስራት።

  • በውክልና ጥምቀቶች ምስክር በመሆን መስራት።

  • ደንበኞችን መርዳት።

የመልከ ጼዴቅ ክህነት ተሸካሚዎች እና በአሮናዊ ክህነት ውስጥ ያሉ ካህናት የሙታን ጥምቀትን እንዲያከናውኑ ሊጋበዙ ይችላሉ። የመልከ ጼዴቅ ክህነት ተሸካሚዎች ለሙታን ማረጋገጫዎችን እንዲሰጡ ሊጋበዙ ይችላሉ።

የቤተመቅደስ የመንፈስ ሥጦታ የተቀበሉ ወንዶች ብቻ የሚከተሉትን ለማድረግ ይጋበዛሉ፦

  • የጥምቀት መዝጋቢ በመሆን ያገለግላል።

  • የማረጋገጫ መዝጋቢ በመሆን ያገለግላል።

28.2.2

የቤተመቅደስ ቡራኬ (የመጀመሪያውን ጨምሮ)

ለሞቱ የውክልና የቤተመቅደስ የመንፈስ ስጦታ በሚከናወንበት ጊዜ የቤተመቅደስ የመንፈስ የስጦታው የመጀመሪያ ክፍል የሚከናወነው እና የሚመዘገበው ለየብቻው ነው (27.2ን ይመልከቱ)። የቤተመቅደስ ቡራኬ የተቀበለ የቤተመቅደስ መግቢያ መታወቂያ ያለው ማንኛውም አባል እነዚህን ሥርዓቶች ለመቀበል ወኪል ሆኖ ሊሰራ ይችላል።

28.2.3

ከትዳር ጓደኛ ጋር መታተም እና ልጆችን ከወላጆች ጋር ማተም

የሞቱ ሰዎች በህይወት እያሉ ካገቧቸው የትዳር ጓደኞቻቸው ጋር በቤተመቅደስ መታተም ይችላሉ። የሞቱ ሰዎች በህይወት ካሉ ወይም ከሞቱ ልጆቻቸው ጋርም መታተም ይችላሉ። የቤተመቅደስ የመንፈስ ስጦታ የተቀበለ ማንኛውም አባል በእትመት ሥርዓቶች ላይ ወኪል ሆኖ ሊሰራ ይችላል።

28.3

ልዩ ሁኔታዎች

ይህ ክፍል በ28.1 ውስጥ ያሉ አንዳንድ መመሪያዎች የማይተገበሩባቸውን ሁኔታዎች ያብራራል።

28.3.1

ከውልደት በፊት የሞቱ ልጆች (ሞተው የተወለዱ እና የጨነገፉ ልጆች)

ከውልደት በፊት ለሞቱ ልጆች የቤተመቅደስ ሥርዓቶች አያስፈልጉም ወይም አይደረጉም። ለተጨማሪ መረጃ 38.7.3ን ይመልከቱ።

28.3.2

ስምንት ዓመት ሳይሞላቸው የሞቱ ልጆች

ትንንሽ ልጆች በኢየሱስ ክርስቶስ የኃጢያት ክፍያ ምክንያት ተቤዥተዋል እንዲሁም “በሰማይ ሰለስቲያል መንግስት ውስጥ [ድነዋል]” (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 137፥10። በዚህ ምክንያት ስምንት ዓመት ሳይሞላቸው ለሞቱ ልጆች ጥምቀት ወይም የቤተመቅደስ የመንፈስ ስጦታ የመቀበል ሥርዓት አይደረግም። ሆኖም፣ በቃል ኪዳኑ ውስጥ ላልተወለዱ ወይም በህይወት እያሉ ያንን ሥርዓት ያልተቀበሉ ልጆች ከወላጆች ጋር ሊታተሙ ይችላሉ (18.1ን ይመልከቱ)።