2010–2019 (እ.አ.አ)
እያንዳንዱ የአሮናዊ ክህነት ስልጣን ያለው ሰው መረዳት የሚገባው ነገር
ሚያዝያ 2018 (እ.አ.አ)


እያንዳንዱ የአሮናዊ ክህነት ስልጣን ያለው ሰው መረዳት የሚገባው ነገር

የእናንተ የአሮናዊ ክህነት ሹመት የእግዚአብሔር ልጆች የክርስቶስን የኃጢያት ክፍያ ሀይል ለመቀበል ዋና ክፍል ነው።

ወንድሞች፣ በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ውስጥ ከእናንተ ጋር በመሆኔ እድለኛ ነኝ። የሚስዮን ፕሬዘዳንት በነበርኩበት ጊዜ፣ የመጀመሪያ የሚስዮን ቡድናችንን ስንቀበል በጣም ደስተኛ ነበርኩኝ። ተጨማሪ ልምምድ ያላቸው አንዳንድ ወንጌል ሰባኪዎች ከእነርሱ ጋር ለትንሽ ጊዜ ለመገናኘት እየተዘጋጁ ነበር። የልጆችን ወንበሮች በግማሽ ክብ እንዳዘጋጁት ተመለከትኩኝ።

“እነዚህ ትንንሽ ወንበሮች ምንድን ነው ነገራቸው” ብዬ ጠየቅኩኝ።

“ለአዲሶቹ ሚስዮኖች ነው” ብለው ሚስዮኖቹ በእፍረት መለሱ።

ሌሎችን የምንመለከትበት መንገድ ማን እንደሆኑ እና ምን እንደሚሆኑ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር አምናለሁ።1 በዛ ቀን ሚስዮኖቻችን በትልቅ ወንበር ላይ ተቀመጡ።

አንዳንድ ጊዜ፣ ለወንድ የአሮን ክህነት ስልጣን ተሸካሚ ወጣቶቻችን እግዚአብሔር ቅዱስ እምነትና ጠቃሚ የሆነ ስራ እንዲሰሩ እንደሰጣቸው እንዲመለከቱ ከመርዳት ይልቅ፣ የህፃን ወንበሮች እንዳንሰጣቸው እፈራለሁ።

ፕሬዘዳን ቶማስ ኤስ ሞንሰን ወጣት ወንዶች “የእግዚአብሔርን ክህነት ተሸካሚ መሆን ምን ማለት እንደሆነ መረዳት እንዳለባቸው መከሩን። ወደተጠሩበት ቅዱሳዊ ጥሪ መንፈሳዊ ግንዛቤ መመራት አለባቸው።”2

ዛሬ፣ መንፈስ ቅዱስ ስለአሮናዊ ክህነት ኃይልና ቅድስና ለበለጠ መረዳት እንዲመራን እጸልያለሁ እንዲሁም በክህነት ሃላፊነታችና ላይ የበለጠ እንድናተኩር እንዲያነሳሳን እጸልያለሁ። መልዕክቴ፣ ለአሮናዊ ክህነት እንዲሁም ለመልከጸዴቅ ክህነት ተሸካሚዎች በሙሉ ነው።

ሽማግሌ ዳለን ጂ ረንለንድ የክህነት አላማ ለእግዚአብሔር ልጆች ለኢየሱስ ክርስቶስ የሃጢያት ክፍያ ኃይል አቅርቦት መስጠት እንደሆነ አስተማሩ።3 የክርስቶስን የሃጢያት ክፍያ ኃይል በሕይወታችን ውስጥ ለመቀበል፣ በእርሱ ማመን፣ ለሃጢያታችን ንስሃ መግባት፣ በስነስርዓቶች አማካኝነት ቅዱስ ቃል ኪዳኖችን መግባትና መጠበቅ፣ እንዲሁም መንፈስ ቅዱስን መቀበል አለብን።4 እነዚህ ነገሮች በአንዴ የምንተገብራቸው መርሆዎች አይደሉም፣ ነገር ግን፣ ወደ ክርስቶስ መጥተን በእርሱ ፍጹማኖች እንሆን ዘንድ በህበረት እርስ በእርሳቸው ላይ በመገንባት ቀጣይነት ባለው ሂደት ውስጥ ይሰራሉ።5

ስለዚህ፣ በዚህ ውስጥ የአሮናዊ ክህነት ሀላፊነት ምንድን ነው? የክርስቶስን የሃጢያት ክፍያ ኃይል አቅርቦት ለማግኘት እንዴት ይረዳናል? የመላዕክቶች አገልግሎትና የማዘጋጃ ወንጌል በሆነው የአሮናዊ ክህነት ቁልፍ ላይ መልሱ እንዳለ አምናለሁ።6

የመላዕክቶች አገልግሎት

በመላዕክቶች አገልግሎት አንድ ክፍል ላይ እንጀምር። የእግዚአብሔር ልጆች በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነት ከሚኖራቸው በፊት፣ ሊያውቁትና ወንጌሉን ሊማሩ ይገባል። ሐዋርያው ፓውሎስ እንዳለው፤

“ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?

“ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ? …

“እምነት ከመስማት ነው፣ መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።”7

ከመጀመሪያ ጊዜ ጀምሮ፣ እግዚአብሔር “… የክርስቶስን መምጣት ለሰው ልጆች ለማሳወቅ መላዕክቶችን ላኳል።”8 መላዕክቶች የእግዚአብሔርን መልዕክት የሚመሰክሩ ከሰማይ ናቸው።9 በእብራይስጥ እና በግሪክ የመልአክ ዋና ቃል ፍቺ “መልዕክተኛ” ማለት ነው።10

መላዕክቶች ቃሉን ሊያውጁ እና እምነትን ሊገነቡ በእግዚአብሔር ጥልጣን ያላቸው መልእክተኞች እንደሆኑ ሁሉ፣ የአሮን ክህነት የምንሸከም ሰዎች “ሁሉንም ለማስተማርና ወደ ክርስቶስ እንዲመጡ ለመጋበዝ”11 ተሸመናል።ወንጌልን መስበክ የክህነት ሃላፊነት ነው። ከዚህ ሃላፊነት ጋር የተገናኘው ኃይል ለነብያቶች ወይም ለሚስዮኖች ብቻ አይደለም። ይህ ለእናንተም ነው!12

ይህን ኃይል እንዴት ነው የምናገኘው? የ12 ዓመት ዲያቆን ወይም አንዳችን እንዴት ነው እምነት በክርስቶስን ወደ እግዚአብሔር ልጆች ልብ የምናመጣው? ኃይሉ በእኛ ውስጥ እንዲሆን ቃሎቹን በማከማቸት እንጀምራለን።13 ይህን ካደረግን “ሰዎች ለማሳመን የእግዚአብሔር ሀይል”14 እንደሚኖረን ቃል ገብቷል። በምልዓተ ጉባኤ ውስጥ ማስተማር ወይም የአባልን ቤት መጎብኘት እድል ሊሆን ይችላል። ከጓደኛ ወይም ከቤተሰባ አባል ጋር መነጋገርን ጨምሮ ትንሽ ኢመደበኛ ሊሆን ይችላል። በእነዚህ ማንኛውም ሁኔታዎች ውስጥ ዝግጁ ከሆንን፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መላዕክቶች እንደሚያስተምሩት ወንጌልን እናስተምራለን።15

ምስል
ጄከብ እና ወንድም ሆልምስ

በቅርብ በፓፑአ ጊኒ የአሮን ክህት ተሸካሚ የሆነውን ጄከብ ስለመጽሐፈ ሞርሞን ኃይል እና መጥፎ ነገርን እንዴት እንደሚቋቋም እና መንፈስን እንዴት እንደሚከተል እንደረዳው ሲመሰክር ሰማሁት። ቃላቶቹ የእኔን እና የሌሎችን እምነት አሳደገ። እንዲሁም የአሮናዊ ክህነት ተሸካሚዎችን ንግግር በሸንጎ ስብሳባዎች ውስጥ ስሰማ እምነቴ አድጓል።

ወጣት ወንዶች፣እናንተ ስልጣን ያላችሁ መልእክተኞች ናችሁ። በቃላቶቻችሁ እና በስራዎቻችሁ በኩል፣ በእግዚአብሔር ልጆች ልብ የክርስቶስን እምነት ለማምጣት ትችላላችሁ።16 ፕሬዘደንት ራስል ኤም. ኔልሰን እንዳሉት፣ “ለእነርሱ እንደአገልጋይ መላእክቶች ትሆናላችሁ።”17

የማዘጋጃው ወንጌል

በክርስቶስ ላይ ያደገ እምነት ሁሌም ወደ መለወጥ መሻትን ወይም ወደ ንስሃ ያመራል።18 ስለዚህ የመላዕክት አገልግሎት ቁልፍ “የንስሃና ጥምቀት እንዲሁም የሃጢያት ስርየት ወንጌል” በሆነው በማዘጋጃ ወንጌል ቁልፍ መከተሉ ተገቢ ነው።19

የአሮናዊ ክሀነት ሃላፊነታችሁን ስታጠኑ፣ ሌሎችን ንስሃ እንዲገቡና እንዲሻሻሉ የሚደነግግ ግብዣን ታያላችሁ።20 ያ በመንደግ ማዕዘን ላይ ቆመን ንስሃ ግቡ እያን መጮኽ ማለት አይደለም! ያ ማለት እኛ ንስሃ እንድንገባ፣ እኛም በይበልጥ ሌሎችን ይቅር እንድንል እና ሌሎችን ስናገለግል ንስሃ የሚያመጣውን ተስፋና ሰላም ስለተለማመድለነው ለሌሎች ማቅረብ ማለት ነው።

የአሮናዊ ክህነት ተሸካዎች የራሳቸውን የምልዓተ ጉባኤ አባሎችን ሲጎበኙ አብሬአቸው ነበርኩኝ። የሳሳ ልባቸውን እንዲሁም ወንድሞቻቸውን የእግዚአብሔርን ፍቅር እንዲሰማቸው ሲረዱ ተመልክቻለሁ። አንድ ወጣት ለጓደኞቹ ስለንስሃ ኃይል ሲመሰክር ሰምቻለሁ። ይህን ሲያደርግ ልቦች ሳሱ፣ ሃላፊነቶች ተደረጉ እንዲሁም የክርስቶስ የፈዋሽነት ኃይል ተሰማ።

ፕሬዘደንት ጎርደን ቢ ሂንክሊ እንዳስተማሩት፥ “ንስሃ መግባት አንድ ነገር ነው። ሃጢያታችን መሻሩ ወይም ይቅር መባሉ ሌላ ነገር ነው። ይህንን የማምጣት ሃይል ያለው የአሮንዊ ክህነት ላይ ነው።”21 የጥምቀትና የቅዱስ ቁርባን የአሮናዊ ክህነት ስነስርዓቶች ለኃጢያት ስርየት የምንገባውን ንስሃችንን ይመለከታሉ እንዲሁም ያጠናቅቃሉ።22 ይህንን ፕሬዘዳንት ዳለን ኤች ኦክስ እንደዚህ ገለፁ፥ “ለሃጢያትችን ንስሃ እንድንገባ እና ወደ ጌታ በተሰበረ ልብና በተዋረደ መንፈስ እንድንመጣ እና ቅዱስ ቁርባን እድንካፈል ታዘናል። … በዚህ መንገድ የጥምቀት ቃልኪዳናችንን ስናድስ፣ ጌታ የጥምቀት ማፅጃ ውጤትን በዳግም ያድሳል።”23

ወንድሞች፣ ይህም በአዳኝ የኃጢያት ክፍያ ሀይል በኩል ንስሀ ለገቡ ልቦች የኃጢያቶች ስርየት ስርዓቶችን የማቅረብ ቅዱስ እድል ነው።24

ቅዱስ ቁርባንን ለመጀመሪያ ጊዜ በመባረክ እራሱን ለመግለጽ ስለተቸገረ ስለ አንድ ካህን ተነገረኝ። ይህን ሲያደርግ ኃይለኛ የሆነ መንፈስ በእሱ እና በታዳሚዎቹ ላይ መጣ። ከዛ በኋላ፣ በዛ ስነስርዓት ላይ ስለተሰማው ስለእግዚአብሔር ኃይል ትንሽ ነገር ግን ግልፅ የሆነ ምስክርነት ሰጠ።

ምስል
የክነት ሸንግ ከምቡሎንጎ ቤተሰብ ጋር

በሲድኒ አውስታሊያ ውስጥ፣ አራት የካህን ክፍል አባሎች የምቡሎንጎ ቤተሰቦችን አጠመቁ። ከእነዚህ ካህናት እናቶች አንዷ አንድ ሀይለኛ አጋጣሚ ልጇን እንዴት እንደነካው ነገረችኝ። እነዚህ ካህናት “በኢየሱስ ክርስቶስ ተመድበው”25 ማለት ምን እንደሆነ ለመረዳት ችለዋል።

በቤተመቅደስ ውስጥ ካህኖች ለሌሎች የመጠመቅ ስነስርዓቶችን መፈጸም እንደሚችሉ ታውቃላችሁ። የ17 ዓመት ወንድ ልጄ ለተወሰኑ ዘሮቼ አጠመቀኝ። ሁለታችንም ለአሮናዊ ክህነት እና ለእግዚአብሔር ልጆች ደህንነት መተግበር መቻል ጥልቅ የሆነ ምስጋና ተሰማን።

ወጣቶች፣በክህነት ሀላፊነቶቻችሁ በትጋት ስታገለግሉ፣ እናንተም “የሰውን አለሟችነት እና የዘለአለም ህይወት ለማምጣት”26 በሆነው በእግዚአብሔር ስራ እየተሳተፋችሁ ናችሁ። እንደእዚህ አይነት ልምምዶች ፍላጎታችሁን ያሳድጉታል እናም እንደ ወንጌል ሰባኪዎች ንስሀ ለማስተማር እና ተቀያሪዎችን ለመጠቅ ያዘጋጇችኋል። እነርሱም ደግሞ በእልከ ጼዴቅ ክህነት ውስጥ ለህይወት ሙሉ አገልግሎት ያዘጋጇችኋል።

መጥምቁ ዮሀንስ፣ ምሳሌአችን

የአሮን ክህነት ተሸካዎች፣ እኛ ከመጥምቁ ዮሐንስ ጋር አገጋዮች የመሆን እድልና ሃላፊነት አለን። ዮሐንስ ስለክርስቶስ እንዲመሰክር እና ሁሉንም ንስሃ እንዲገቡ እና እንዲጠመቁ እንዲጋብዝ ስልጣን እንደተሰጠው መልዕክተኛ ተላከ። ያ ማለት ስለተወያየንበት የአሮናዊ ክህነት ቁልፍ ተለማመደ ማለት ነው። ዮሐንስ ከዚያም አወጀ፣ “እኔስ ለንስሃ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፣ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ … እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳት ያጠምቃችኋል”27

ስለዚህ የአሮናዊ ክህነት፣ ከመላዕክት አገልግሎት ጋር፣ የማዘጋጃ ወንጌሉን ማገልገል፣ ለእግዚአብሔር ልጆች በመልከጸዴቅ ክህነት አማካኝነት በዚህ ሕይወት ውስጥ ከምንቀበላቸው ታላቅ ስጦታዎች ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን እንዲቀበሉ መንገዱን ያዘጋጃል።28

ለአሮናዊ ክህነት ተሸካዎች እግዚአብሔር ምን ዓይነት ከፍተኛ ሃላፊነትን ነው የሰጠው!

ግብዣና ቃል-ኪዳን

ወላጆችና የክህነት ተሸካሚዎች፣ የፕሬዘዳንት ሞንሰንን “የእግዚአብሔርን ክህነት ተሸካሚ መሆን ምን ማለት እንደሆነ” የሚለውን ምክር ጠቀሜታ ይሰማችኋን?29 የአሮናዊ ክህነትን መረዳት እና ማጉላት አማኝ የመልከጸዴቅ ክህነት ተሸካሚዎች፣ ኃይል የተሞሉ ሚስዮኖች እና ፃድቅ ባሎችና አባቶች እንዲሆኑ ልንሰጣቸው የምንችለው ማዘጋጃ ነው። በአገልግሎታቸው አማካኝነት፣ ለእግዚአብሔር ልጆች ደህንነት በክርስቶስ ስም የመተግበር የክህነት ኃይልን እውንነት ይረዳሉ እናም ይሰማቸዋል።

ወጣት ወንዶች፣ እግዚአብሔር ለእናንተ ስራ አለው።30 የእናንተ የአሮናዊ ክህነት ሹመት የእርሱ ልጆች የክርስቶስን የሃጢያት ክፍያ ኃይል ለመቀበል የመርዳት ማዕከላዊ ነው። እነዚህን ቅዱስ ሃላፊነቶች የሕይወታችሁ ማዕከላዊ ስታደርጉት የእግዚአብሔርን ኃይል በበለጠ እንደሚሰማችሁ ቃል እገባለሁ። ስራውን እንዲተገብር ቅዱስ በሆነ ጥሪ እንደተጠራ እንደ እግዚአብሔር ልጅ ማንነታችሁን ትረዳላችሁ። እናም፣ እንደ መጥምቁ ዮሀንስ፣ለልጁ መምጣት መንገድን ታዘጋጃላችሁ። ስለዚህ እውነታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እመሰክራለሁ፣ አሜን።

ማስታወሻዎች

  1. የህ ሙሴ ላይ የተከሰተ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ካደረገው ግንኙነት በኋላ፣ እራሱን ለየት ባለ መልኩ ማየት ጀመረ - እንደ እግዚአብሔር ልጅ። ይህ ዕይታው “የሰው ልጅ” (ሙሴ 1፥1–20 ተመልከቱ) ብሎ የጠራውን የሴጣንን እንዲቋቋም እረዳው። ደግሞም ቶማስ ኤስ. ሞንሰን፣ “ሌሎችን እንደሚሆኑት ተመልከቷቸው,” Liahona, ህዳር 2012 (እ.አ.አ)፣68–71፤ ዴል ጂ. ረንለንድድ፣ “በእግዚአብሔር አይኖች በኩል” Liahona, ህዳር 2015 (እ.አ.አ)፣ 93–94 ይመልከቱ።

  2. Thomas S. Monson, general conference leadership meeting, Mar. 2011.

  3. ዴል ጂ. ረንለንድ, “ክህነት እና የአዳኙ የኃጢያት ክፍያ ሀይል፣” Liahona, ህዳር 2017 (እ.አ.አ)፣ 64–67።

  4. 2 ኔፊ 31–323 ኔፊ 11፥30–4127፥13–21ኤተር 4፥18–19ሙሴ 6፥52–68; 8፥24 ተመልከቱ።

  5. ሞሮኒ 10፥32፤ ደግሞም Preach My Gospel: A Guide to Missionary Service (2004)፣ 6 ተመልከቱ።

  6. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 13፥184፥26107፥20 ተመልከቱ።

  7. ሮሜ 10፥14–15፣17። ጆሴፍ ስሚዝ ተመሳሳይ እውነታን አስተማረ፥ “እምነት በእግዚአብሔር አገልጋዮች ምስክርነት አማካኝነት የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ይመጣል፤ ያ ምስክርነት ሁሌም በትንቢት እና በራዕይ መንፈስ ይታገዛል” (Teachings of Presidents of the Church: Joseph Smith [2007], 385)።

  8. ሞሮኒ 7፥22አልማ 12፥28–3013፥21–2432፥22–2339፥17–19ሔላማን 5፥11ሞሮኒ 7፥21–25፣ 29–32ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፥3529፥41–42ሙሴ 5፥58ማቴዎስ 28፥19ሮሜ 10፥13–17 ይመልከቱ።

  9. See George Q. Cannon, Gospel Truth, sel. Jerreld L. Newquist (1987), 54.

  10. See James Strong, The New Strong’s Exhaustive Concordance of the Bible (1984), Hebrew and Chaldee dictionary section, 66, Greek dictionary section, 7.

  11. ትምህርት እና ቃልኪዳኖች 20፥59

  12. ሔንሪ ቢ. አይሪንግ፣ “እርሱም ይጠነክር ዘንድ፣” Liahona, ህዳር. 2016 (እ.አ.አ) 75–78 ተመልከቱ፤ አልማ 17፥3ሔላማን 5፥186፥4–5ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 28፥3

  13. 1 ዮሀንስ 2፥14አልማ 17፥226፥1332፥42።  Fulfilling My Duty to God: For Aaronic Priesthood Holders ይህን ለማከናወን የሚረዳ ዋጋ ያለው መሳሪያ ነው።

  14. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 11፥21፤ደግሞም ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 84፥85 ተመልከቱ።

  15. 2 ኔፊ 32፥3ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 42፥1450፥17–22 ተመልከቱ።

  16. ሞሮኒ 7፥25 ተመልከቱ።

  17. Russell M. Nelson, “Honoring the Priesthood,” Ensign, May 1993, 40፤ ደግሞም አልማ 27፥4 ይመልከቱ።

  18. አልማ 34፥17ሔላማን 14፥13 ተመልከቱ።

  19. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 84፥27

  20. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፥46፣ 51–59፣ 73–79 Fulfilling My Duty to God: For Aaronic Priesthood Holders ይህን ሀልፊነቶቻችንን እንድንረዳ የሚረዳን አስፈላጊ መሳሪያ ነው።

  21. Gordon B. Hinckley, “The Aaronic Priesthood—a Gift from God,” Ensign, May 1988, 46.

  22. ሽማግሌ ዲ. ቶድ ክርስቶፈርሰን እንደገለጹት፥ “የውኃ ጥምቀት በንስሃ ሂደት ውስጥ የመጨረሻው ወይም አክሊል የመድፊያ ደረጃ ነው። የሃጢያት ኑዛዜ ከቃልኪዳን ታዛዥነታችን ጋር ንስሃችንን ሙሉ ያደርጋል፤ በእርግጥ ንስሃ ካለ ቃኪዳን ያላለቀ ይሆናል” (“በክርስቶስ እምነትን መገንባት፣” Liahona, መስከረም 2012 (እ.አ.አ)፣ 14–15)። ደግሞም ዲ. ቶድ ክርስቶፈርሰን፣ “ንስሀ የመግባት መለኮታዊ ስጦታ,” Liahona, ህዳር 2011 (እ.አ.አ)፣ 38–41፤ የጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም፣ ማቴዎስ 26፥24 (in the Bible appendix) ይመልከቱ።

    የቅዱስ ቁርባን ስነስርዓት በእያንዳንዱ ሳምንት የአዳኙን የሃጢያት ክፍያ ጸጋ በተመሳሳይ የጥምቀት እና የማረጋገጫ ማጽጃ የሚፈቅድልንን ቅዱስ ቃልኪዳኖች እንድናድስ እድል እንደሚሰጠን አስተማሩ” (“Understanding Our Covenants with God,” Liahona, July 2012, 21). See also Dallin H. Oaks, “Always Have His Spirit,” Ensign, Nov. 1996, 59–61 ተመልከቱ።

  23. Dallin H. Oaks, “The Aaronic Priesthood and the Sacrament,” Liahona, Jan. 1999, 44.

  24. ሽማግሌ ዴቪድ ኤ. ቤድናር እንደገለጹት፥ “የደህንነት እና የማደግ ስነስርዓት በጌታ መልሶ የተቋቋመ ቤተክርስቲያን ውስጥ ከሃይማኖታዊ ወይም ከምልክታዊ ትዕይንት ይበልጥ የዘለለ ነው። ይልቁንስ የሰማይ በረከትና ኃይል በግል ሕይወታችን ውስጥ መፍሰስ እንዲችል ስልጣን ያላቸውን መስመሮች ያካትታሉ” (“Always Retain a Remission of Your Sins፣” Liahona፣ ግንቦት 2016 (እ.አ.አ)፣ 60)።

  25. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፥73

  26. ሙሴ 1፥39

  27. ማቴዎስ 3፥11

  28. ብዙ የቤተክርስቲያን መሪዎች መንፈስ ቅዱስን እንደ ምድራዊ ታላቅ ስጦታ ፈርጀውታል።

    ፕሬዘዳንት ዳለን ኤች ኦክስ እንዲህ አሉ፣ “በዚህ ምድር ላይ ቀጣይነት ያለው የመንፈስ ቅዱስ ጓደኝነት መኖር ማለት በጣም እንቁ የሆነ ሃብት ነው።” (“The Aaronic Priesthood and the Sacrament፣” Liahona፣ ጥር 1999 (እ.አ.አ)፣ 44)።

    ሽማግሌ ብሩስ አር. መካንኪ እንዳሉት፥ “ከዘላለማዊነት አንጻር ስንናገር፣ የዘላለም ሕይወት ከእግዚአብሔር ስጦታዎች ሁሉ ታላቁ ስጦታ ነው። ነገር ግን የዚህን ሕይወት ብቻ አጥበን ስንመለከት፣ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ሟች የሆነ ሰው ሊደሰትበት የሚችል ታላቅ ስጦታ ነው” (“What Is Meant by ‘The Holy Spirit’?” Instructor, Feb. 1965, 57)።

    ፕሬዘደንት ዊልፈርድ ዎድረፍ እንዳሉት፥ “መንፈስ ቅዱስ ከእናንተ ጋር ከሆነ—እናም እያንዳንዳችሁ ሊኖራችሁ ይገባኋል—ለእናንተ ከዚህ የበለጠ ምንም ስጦታ፣ ምንም ታላቅ የሆነ በረከት፣ ምንም ታላቅ የሆነ ምስክርነት ለማንም ሰው በምድር ላይ አይሰጥምእላችኋለሁ።. መላእክት ያገለግሏችኋል፤ ብዙ ታዕምራቶች ታያላችሁ፤ በምድር ውስት ብዙ ድንቆች ታያላችሁ፤ ነገር ግን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ለኦች ከሚሰጥ ስጦታ በላይ ታላቅ ነውብዬ አውጃለሁ” (Teachings of Presidents of the Church: Wilford Woodruff [2004], 49)።

    ሽማግሌ ዴቪድ ኤ. ቤድናር እንዳስተማሩት፥ “የምንታዘዘው የእግዚአብሔር ትዕዛዝ እና የምንከተለው የተነሳሱ የቤተክርስቲያን መሪዎች ምክር በቀዳሚነት የመንፈስ ቅዱስን ጓደኝነት የማግኘት ሁኔታ ላይ ያተኩራል። ሁሉም የወንጌል ትምህርቶች እና እንቅስቃሴዎች ወደ ክርስቶስ በመምጣት በሕይወታችን ውስጥ መንፈስ ቅዱስን በመቀበል ላይ ማዕከላዊ ያደረጉ ናቸው።” (“መንፈስ ቅዱስን መቀበል፣” Liahona፣ ህዳር 2010 (እ.አ.አ)፣ 97)።

  29. Thomas S. Monson, general conference leadership meeting, Mar. 2011.

  30. ሙሴ 1፥6 ተመልከቱ።