ምዕራፍ ፳
የአሶር መጥፋት ኃጢአተኞች በዳግም ምፅአት እንደሚጠፉት ምሳሌ ነው—ጌታ እንደገና ከመጣ በኋላ ጥቂት ሰዎች ይቀራሉ—የያዕቆብ ቅሪቶች በዚያን ቀን ይመለሳሉ—ኢሳይያስ ፲ን አነጻፅሩ። ከ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ ጻድቅ ያልሆኑ ሕጎችን ለሚደነግጉ፣ የጻፉአቸውን የግፍን ትእዛዛት ለሚያዝዙ ወዮላቸው፤
፪ ሀፍትህ የሚፈልጉትን ለመከልከል፣ እናም የድሃ ሕዝቦቼን መብት ለመውሰድ፣ ለመበለቶችንም ሰለባቸው እንዲሆኑላቸው፣ እናም አባት አልባዎችን ለመዝረፍ ዘንድ የግፍን ትእዛዛት አዝዘዋል!
፫ እናም ከሩቅ በሚመጡት ሀበመጎብኘታችሁና በመውደሚያችሁ ቀን ምን ታደርጋላችሁ? ለእርዳታስ ወደ ማን ትሸሻላችሁ? ክብራችሁንስ ወዴት ትተዋታላችሁ?
፬ ከእኔ ውጭ ከእስረኞች በታች ይጎነበሳሉ፣ በሚገደሉትም መካከል ይወድቃሉ። በዚህም ሁሉ እንኳን ጌታ ቁጣው አልበረደችም፣ ነገር ግን አሁንም ገና እጁ ተዘርግታለች።
፭ ሶርያ ሆይ፣ የቁጣዬ በትር፣ እናም በእጃቸው ያለው መሳሪያ ሀቁጣቸው ነው።
፮ ሀበግብዝ ሀገሮችም መካከል እልከዋለሁ፣ እናም ምርኮንና ብዝበዛውንም ይወስድ ዘንድ፣ እና እንደ አደባባይ ጭቃ የተረገጡ ይሆኑ ዘንድ በተቆጣሁአቸው ህዝብ ላይ እልከዋለሁ።
፯ ነገር ግን እርሱ ይህን አላቀደውም፣ ልቡም ቢሆን እንደዚህ አያስብም፤ በልቡ ውስጥ ያለው ግን ብዙ ሀገሮችን ለማጥፋትና ለመቁረጥ ነው።
፰ እንዲህ ይላል፥ መሳፍንቶቼ ሁሉ ነገሥታት አይደሉምን?
፱ ካልኖ እንደ ከርከሚሽ አይደለችምን? ሐማትስ እንደ አርፋድ አይደለችምን? ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደለችምን?
፲ የተቀረፁ ምስሎቻቸው ከኢየሩሳሌምና ከሰማርያ ምስሎች የበለጡትን፣ የጣዖቶችን መንግስታት ሀእጄ እንዳገኘች፤
፲፩ በሰማርያና በጣዖቶቿ እንደአደረግሁት በኢየሩሳሌምና በጣዖቶቿ አላደርግምን?
፲፪ ስለዚህ እንዲህ ይሆናል ጌታ ስራውን በሙሉ በፅዮን ተራራና በኢየሩሳሌም ሲፈፅም፣ ሀየአሶርን ንጉስ የኩሩ ልብ ለፍሬውን የዐይኑንም ከፍታ ትምክህት እቀጣለሁ።
፲፫ ሀእርሱ እንዲህ ብሎአልና፤ በእጄ ጥንካሬና በጥበቤ እነዚህን ነገሮች አድርጌአለሁ፤ እኔ አስተዋይ ነኝና፤ የህዝቦችንም ድንበር ገፋሁ፣ ሀብታቸውንም ዘረፍኩ፣ እናም እንደ ጀግና ሆኜ ፍጥረታትን አጠቃሁ፤
፲፬ እናም እጄ የህዝብን ሀብት እንደ ወፍ ጎጆ አገኘች፤ እና በሰው የተተዉትን እንቁላሎች እንደሚሰበስብ እኔም ደግሞ ምድርን በሞላ ሰበሰብኩ፤ ክንፉን የሚያራግብ፣ ወይም አፉን የሚከፍትም ሆነ የሚጮህ ማንም የለም።
፲፭ ሀምሳር የሚጠቀምበትን ሰው እበልጣለሁ ብሎ ለይመካልን? ወይስ መጋዝ በሚስበው ላይ እራሱን ያጎላልን? በትርስ በራሱ ያለእጅ እራሷን እንደምትነቀንቅ ወይንም ከዘራ እንጨት እንዳልሆነ ሁሉ እራሱን እንደሚያነሳ!
፲፮ ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ፣ በወፍራሞቹ ላይ መክሳትን ይልካል፣ ሀከክብሩም በታች እንደ እሳት መቃጠል የሆነ ቃጠሎን ያስነሳል።
፲፯ እናም የእስራኤል ብርሃን ለእሳት ይሆናል፣ ቅዱሷም ነበልባል ይሆናል፣ እሾሁንና ኩርንችቱንም በአንድ ቀን ያቃጥለዋል፣ ይበላዋልም፤
፲፰ እናም የዱሩንም፣ የፍሬያማውን ሜዳ፣ ክብሩንም፣ ነፍሱንና ስጋውንም ሀያቃጥለዋል፤ እነርሱ አርማ ተሸካሚው እንደ ወደቀ ይሆናሉ።
፲፱ እናም ሀየተቀሩትም የዱር ዛፎቹ ህፃን መቁጠር እስኪችላቸው ድረስ ትንሽ ይሆናሉ።
፳ እናም ሀበዚያ ቀን እንዲህ ይሆናል፣ የእስራኤል ቅሪት፣ እናም ለከያዕቆብ ቤት የዳኑት፣ ከእንግዲህ ወዲህ በዚያ በመታቸው ላይ ሐአይቆዩም፣ ነገር ግን በጌታ በእስራኤሉ ቅዱስ በእውነት ይመካሉ።
፳፩ ሀቅሪቶች ይመለሳሉ፣ አዎን፣ የያዕቆብም ቅሪቶች ቢሆኑ እንኳ፣ ወደ ኃያሉ እግዚአብሔር ይመለሳሉ።
፳፪ እስራኤል ሆይ ህዝብሽ እንደ ባህር አሸዋ የበዛ ቢሆንም እንኳ፣ ቅሪቶቻቸው ይመለሳሉ፤ የተነገረውም ሀጥፋት በፅድቅ ለይትረፈረፋል።
፳፫ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ያለቀ ሀየተቈረጠ ነገርን በምድር ሁሉ መካከል ይፈጽማል።
፳፬ ስለዚህ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል—በፅዮን የምትኖሩ ህዝቤ ሆይ፣ አሶርን አትፍራው፤ በበትር ይመታሀል፣ ግብፅም ሀእንዳደረገው ዘንጉን ያነሳብሀል።
፳፭ ቁጣዬ እስኪፈፀም መዓቴም እስኪያጠፋቸው ጥቂት ጊዜ ቀርቷል።
፳፮ እናም የሰራዊት ጌታ ሀምድያምን በሔሬብ አለት በኩል እንደመታው ጅራፍ ያነሳበታል፣ በትሩም በባህር ላይ ይሆናል፣ በግብፅም እንዳደረገው ያነሳዋል።
፳፯ እናም እንዲህ ይሆናል፣ በዚያን ቀን ሀሸክሙ ከትከሻህ ላይ ይነሳል፣ ቀንበሩም ከአንገትህ ላይ ይወርዳል፣ ለከቅባቱም የተነሳ ቀንበሩም ይጠፋል።
፳፰ ወደ አንጋይ ሀመጥቷል፣ በሜጌዶን አልፏል፤ በማክማስም እቃውን አስቀምጧል።
፳፱ እነርሱ መተላለፊያውን አልፈዋል፤ ማረፊያቸውንም በጌባ አድርገዋል፤ ራማትም ፈርታለች፤ የሳኦል ጊብአም አምልጣለች።
፴ የጋሊም ልጅ ሆይ፤ ደሀዋ አናቶት ሆይ፣ ለሌሳ እንኳን እስኪሰማ ድረስ ድምፅሽን ከፍ አድርጊ።
፴፩ መደቤና ሸሽታለች፤ የግቤር ህዝቦችም ሊያመልጡ እራሳቸውን ሰብስበዋል።
፴፪ ነገር ግን በዚያን ቀን በኖብ ላይ ይቀራል፤ በፅዮን ሴት ልጆች ተራራ በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጆቹን ያነቃንቃል።
፴፫ እነሆ፣ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ ቅርንጫፎቹን በሚያስፈራ ኃይል ይቆርጣቸዋል፤ እናም በቁመናቸው ሀከፍ ያሉት ይቆረጣሉ፤ እብሪተኞቻቸው ዝቅ ይላሉ።
፴፬ ጥቅጥቅ ያለውንም ጫካ እርሱ በብረት ይቆርጠዋል፣ ሊባኖስም በኃይለኛው እጅ ትወድቃለች።