የሚስዮን ጥሪዎች
ምዕራፍ 3:- ለመጠመቅ እና ማረጋገጫን ለመውሰድ ግብዣ


ምዕራፍ 3፥ ለመጠመቅ እና ማረጋገጫን ለመውሰድ ግብዣ ወንጌሌን ስበኩ፡ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል የማካፈል መመርያ 2023 (እ.አ.አ)

ለመጠመቅ እና ማረጋገጫን ለመውሰድ ግብዣ ወንጌሌን ስበኩ

ምዕራፍ 3

ለመጠመቅ እና ማረጋገጫን ለመውሰድ ግብዣ

ምስል
ወደ እግዚአብሔር በረት ኑ በዋልተር ራኔ

የትምህርት መሰረት

ሁላችንም የሰማይ አባት ልጆች ነን። ወደ ምድር የመጣነው ለመማር፣ ለማደግ እና እሱን ለመምሰል እድል በማግኘት ወደ እርሱ መገኘት መመለስ እንድንችል ነው (ሙሴ 1፡39 ተመልከቱ)። ያለ መለኮታዊ እርዳታ እርሱን መምሰል ወይም ወደ እርሱ መመለስ አንችልም። የሰማይ አባታችን ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን የላከው የሃጢያት ክፍያ እንዲከፍል እና የሞትን እስራት እንዲሰብር ነው (3 ኔፊ 27፡13–22 ተመልከቱ)።

በእርሱ በማመን፣ ንስሐ በመግባት፣ በመጠመቅ፣ በማረጋገጫ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ በመቀበል እና እስከ መጨረሻ በመጽናት የክርስቶስን የመቤዠት ኃይል እናገኛለን። የጥምቀት ቃል ኪዳንን መጠበቅ መንፈስ ቅዱስ ተፈጥሮአችንን እንዲያነጻ፣ እንዲያጠነክር እና ለተሻለ ሁኔታ እንዲለውጥ ራሳችንን ከእግዚአብሔር ጋር ለማገናኘት የመጀመሪያው እርምጃ ነው። ይህንን የሚቀድስ ተጽእኖ መለማመድ በመንፈስ ዳግም መወለድ ይባላል። (2 ኔፊ 31፡7፣ 13–14፣ 20–21ሞዛያ 5፡1–71827፡243 ኔፊ 27፡20ዮሐንስ 3፡5 ተመልከቱ።)

በመንፈስ ዳግም መወለድ የሚጀምረው በውሃ እና በመንፈስ ስንጠመቅ ነው። ጥምቀት አስደሳች እና ተስፋ ሰጪ ሥርዓት ነው። በተሰበረ ልብ እና መንፈስ ስንጠመቅ፣ በእግዚአብሔር ድጋፍ ኃይል ሕይወትን እንደ አዲስ እንጀምራለን። ከተጠመቅን እና የመንፈስ ቅዱስ ማረጋገጫ ከተቀበልን በኋላ፣ ቅዱስ ቁርባንን በተገቢው መንገድ በመካፈል በመጠንከር መቀጠል እንችላለን። (2 ኔፊ 31፡13ሞዛያ 18፡7–16ሞሮኒ 6፡2ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፡37 ተመልከቱ።)

መጋበዝ

የመንፈስ ምሪት ሲሰማችሁ፣ ሰዎች እንዲጠመቁ እና ማረጋገጫ እንዲወስዱ ጋብዙ። ይህ በማንኛውም ትምህርት ጊዜ ሊከሰት ይችላል።

የጥምቀትን ትምህርት አስተምሩ እንዲሁም ሰዎች የክርስቶስን ትምህርት እንዲረዱ እርዷቸው (ትምህርት 3ን ተመልከቱ)። ስለ ጥምቀት ቃል ኪዳን አስፈላጊነት እና ደስታ፣ የኃጢያት ስርየት ስለማግኘት እና የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ በማረጋገጫ ስለመቀበል አስተምሩ።

ያስተማራችሁትን እና የሚገቡትን ቃል ኪዳን መረዳታቸውን በማረጋገጥ ሰዎችን ለጥምቀት ግብዣ አዘጋጁ። የጥምቀት ቃል ኪዳን እንደሚከተለው ነው:-

  • የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በእኛ ላይ ለመውሰድ ፈቃደኛ መሆን።

  • የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት መጠበቅ።

  • እግዚአብሔርን እና ሌሎችን ማገልገል።

  • እስከ መጨረሻው መጽናት። (ትምህርት 4ን ተመልከቱ።)

የሚከተለውን ማጋራት ትችላላችሁ፥

“ስንጠመቅ፣ ‘[እንደምናገለግል] እና ተዕዛዛቱን እንደምንጠብቅ በፊቱ እንደምስክርነት ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን እንገባለን’። ይህንን ቃል ኪዳን ስንገባ፣ ‘መንፈሱን በብዛት [በእኛ ላይ] [እንደሚያፈስ][ ቃል ገብቷል” (ሞዛያ 18፡10)።

ለጥምቀት የምታቀርቡት ግብዣ ግልጽና ቀጥተኛ መሆን አለበት። እንዲህ ልትሉ ትችላላችሁ፡-

“ይህን ሥርዓት ለመፈጸም በተሾመ ሰው በመጠመቅ የኢየሱስ ክርስቶስን ምሳሌን ይከተላሉ? ለጥምቀት ለመዘጋጀት እንረዳዎታለን። በ [በተሰጠ ቀን] ዝግጁ መሆን እንደሚችሉ እናምናለን። በእዚያ ቀን ለመጠመቅ ራስዎትን ያዘጋጃሉ?

እንደ ማንኛውም ግብዣ፣ ለመጠመቅ እና ተያያዥ ቃል ኪዳኖችን ሲጠብቁ ሰዎች የሚያገኟቸውን ታላቅ በረከቶች ቃል ግቡ። የእነዚህን በረከቶች ምስክርነት አካፍሉን።

ጥምቀት እና የመንፈስ ቅዱስ ማረጋገጫ የመጨረሻ መድረሻ እንዳልሆኑ አስተምሩ። ይልቁንም፣ ተስፋን፣ ደስታን፣ እና የእግዚአብሔርን ሀይል ወደ ግለሠቡ ህይወት ይበልጥ በሚያመጣ የለውጥ መንገድ ላይ ያሉ ናቸው (ሞዛያ 27፡25–26 ተመልከቱ)። ሰዎች ከተጠመቁ እና ማረጋገጫ ከተቀበሉ በኋላ፣ በቃል ኪዳኑ መንገድ ሲሄዱ በመንፈስ ለመቀደስ ሊጠባበቁ ይችላሉ።

የሚቻል ከሆነ የምታስተምሯቸውን ሰዎች በጥምቀት አገልግሎት እና በቅዱስ ቁርባን ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ጋብዙ።

ለጥምቀት ግብዣ ሀሳቦች

ስለ ኢየሱስ ጥምቀት የሚገልጸውን ጥቅስ ለማንበብ አስቡ (ማቴዎስ 3፥13–17 ተመልከቱ)። እንዲሁም የአዳኙን ጥምቀት በየመጽሐፍ ቅዱስ ቪዲዮ ላይ ወይም ደቀ መዛሙርቱ ሲያጠምቁ የሚያሳይ የመፅሐፈ ሞርሞን ቪዲዮን ማሳየት ትችላላችሁ።

እንዲሁም የኔፊን የኢየሱስን ጥምቀት ታሪክ ማንበብ ትችላላችሁ (2 ኔፊ 31፥4–12 ተመልከቱ)። ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት የሚናገሩትን ዘገባዎች ማንበብ የሚማሩትን ሊያበረታታ ይችላል።

የቅዱስ መጽሀፍ ጥናት

የሚከተሉትን ቅዱስ ጥቅሶች አጥኑ፦

ስለተማራችሁት ነገር ማጠቃለያ ጻፉ።