የጥናት እርዳታዎች
ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፲፯


ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፲፯፥፲–፲፬።ማቴዎስ ፲፯፥፲፩–፲፫ ጋር አነጻፅሩ

ኢየሱስ አንዱ ለማዘጋጀት እና አንዱ ዳግም ለመመለስ፣ ስለሚያደርጉት ሁለት ኤልያሶች አስተማረ።

ኢየሱስም መለሰ እና እንዲህ አላቸው፣ ኤልያስማ አስቀድሞ ይመጣል፣ እና በነብያት እንደተጻፈው ሁሉንም ነገሮች ደግሞ ይመልሳል።

፲፩ እንደገናም እላችኋለሁ፣ እነሆ፣ መልእክተኛዬን እልካለሁ፣ እና እርሱም መንገዴን በፊቴ ያዘጋጃል ተብሎ ስለእርሱ የተጻፈበት ኤልያስ ከዚህ በፊት መጥቷል፤ የወደዱትንም ሁሉ አደረጉበት እንጂ አላወቁትም።

፲፪ እንዲሁም ደግሞ የሰው ልጅ ከእነርሱ መከራ ይቀበላል።

፲፫ ነገር ግን እላችኋለሁ፣ ኤልያስ ማን ነው? እነሆ፣ መንገዴን በፊቴ እንዲያዘጋጅ የላኩት፣ ይህም ኤልያስ ነው።

፲፬ በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ፣ እና ደግሞም በነቢያት እንደተጻፈው መጥቶ ሁሉንም ነገሮች ዳግሞ ስለሚመልሰው እንደ ነገራቸው አስተዋሉ።