የጥናት እርዳታዎች
ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፳፯


ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፳፯፥፫–፮።ማቴዎስ ፳፯፥፫–፭ከሐዋርያት ስራ ፩፥፲፰ ጋር አነጻፅሩ

የይሁዳ ሞት ተገልጿል።

በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደ ተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ፣ እና ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ፣

ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ።

እነርሱ ግን ለእርሱ እንዲህ አሉት፣ እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ፤ ኃጢያትህም በራስህ ላይ ይሁን።

እና ብሩንም በቤተ መቅደስ ጣለ፣ እና ሄደና እራሱን በዛፍ ላይ አነቀ። ወዲያውም ወደቀ፣ እና ከመካከሉ ተሰነጠቀ አንጀቱም ሁሉ ተዘረገፈ፣ ሞተም።