የጥናት እርዳታዎች
ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፮


ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፮፥፲፬።ማቴዎስ ፮፥፲፫ ጋር አነጻፅሩ፤ በሉቃስ ፲፩፥፬ም እንደዚህ አይነት ቅያሬዎች ነበሩ

ጌታ ወደ ፈተና አይመራንም።

፲፬ ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና ለመግባት እንዳንመራ አትፍቀድልን።

ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፮፥፳፪።ማቴዎስ ፮፥፳፪ ጋር አነጻፅሩ

አይኖቻችን ለእግዚአብሔር ክብር የቀኑ ከሆኑ፣ ሰውነቶቻችን በሙሉ በብርሀን ይሞላሉ።

፳፪ የሰውነት መብራት ዓይን ናት፤ ዓይንህ እንግዲህ ለእግዚአብሔር ክብር የቀናች ብትሆን፣ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል።

ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፮፥፳፭–፳፯።ማቴዎስ ፮፥፳፭፲፥፲ ጋር አነጻፅሩ

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ስለስራቸው አስቸጋሪነት አስጠነቀቃቸው ነገር ግን መንገድን እንደሚያዘጋጅላቸው እና የሰማይ አባት እንደሚሰጣቸው ቃል ገባ።

፳፭ እንደገናም እላችኋለሁ፥ ወደ አለም ሂዱ፣ እናም ስለአለም አታስቡ፤ ምክንያቱም አለም ይጠላችኋል፣ እናም ይሰድዳችኋል፣ እናም ከምኩራባችሁ ያስወጧችኋል።

፳፮ ይህም ቢሆን፣ ህዝብን በማስተማር ከቤት ወደቤት ትሄዳላችሁ፤ እኔም በፊታችሁ እሄዳለሁ።

፳፯ እናም የሰማይ አባትችሁ ለምግብ ምንም የሚያስፈልጋችሁን፣ ምን እንደምትበሉ ይሰጣችኋል፤ እና ለመሸፈኛም፣ የምትለብሱትንም።

ጆ.ስ.ት.፣ ማቴዎስ ፮፥፴፰።ማቴዎስ ፮፥፴፫ ጋር አነጻፅሩ

መጀመሪያ የእግዚአብሔርን መንግስት ለመገንባት መፈለግ ይገባናል።

፴፰ ስለዚህ፣ የዚህን አለም ነገሮች አትፈልጉ ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመገንባት፣ እና ጽድቁንም ለመመስረት ፈልጉ፣ እና እነዚህ ነገሮች ሁሉ ይጨመርላችኋል።