ጴጥሮስ
በአዲስ ኪዳን ውስጥ፣ በቅፍርናሆም ከሚስቱ ጋር ይኖር የነበረ የቤተሳይዳ አሳ አጥማጅ ጴጥሮስ በመጀመሪያ ስምዖን (፪ ጴጥ. ፩፥፩) ተብሎ ይታወቅ ነበር። ኢየሱስ የጴጥሮስን ባለቤት እናትን ፈወሰ (ማር. ፩፥፳፱–፴፩)። ጴጥሮስ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር የኢየሱስ ክርስቶስ ድቀ መዛሙርት እንዲሆን ተጠርቶ ነበር (ማቴ. ፬፥፲፰–፳፪፤ ማር. ፩፥፲፮–፲፰፤ ሉቃ. ፭፥፩–፲፩)። “ገላጭ” ወይም “አለት” የሚል ትርጉም ያለው ኬፋ የሚባለው ስሙ ለእርሱ በጌታ የተሰጠው ነበር (ዮሐ. ፩፥፵–፵፪፤ ጆ.ስ.ት.፣ ዮሐ. ፩፥፵፪ [ተጨማሪ])። አዲስ ኪዳን የጴጥሮስን አንዳንድ ስጋዊ ደካማነቶችን ቢጠቅስም፣ ይህም እነዚህን እንዳሸነፈና በኢየሱስ ክርስቶስ በነበረው እምነት ጠንካራ እንደሆነ ያሳያሉ።
ጴጥሮስ ኢየሱስ ክርስቶስ እና የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መሰከረ (ዮሐ. ፮፥፷፰–፷፱)፣ እናም ጌታ የመንግስትን ቁልፎች በምድር ላይ እንዲይዝ መረጠው (ማቴ. ፲፮፥፲፫–፲፱)። በመቀየሪያ ተራራ ላይ፣ ጴጥሮስ የተቀየረውን አዳኝ፣ እናም ሙሴንና ኢልያ (ኤልያስን) አየ (ማቴ. ፲፯፥፩–፱)።
ጴጥሮስ በጊዜው ዋና ሐዋሪያ ነበር። ከአዳኝ ሞት፣ ትንሳኤ፣ እና ማረግ በኋላ፣ ቤተክርስቲያኗን ሰበሰበ እና የአስቆሮቱ ይሁዳን ለመተካት ሐዋሪያ እንዲመረጥ መመሪያ ሰጠ (የሐዋ. ፩፥፲፭–፳፮)። ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ከተወለደ ጊዜ ጀምሮ ሽባ የነበረ ሰውን ፈወሱ (የሐዋ. ፫፥፩–፲፮) እናም ከእስር ቤት በተአምራት ተለቀቁ (የሐዋ. ፭፥፲፩–፳፱፤ ፲፪፥፩–፲፱)። በጴጥሮስ አገልግሎት ነው ወንጌሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአህዛቦች የተከፈተው (የሐዋ. ፲–፲፩)። በኋለኛው ቀናት፣ ጴጥሮስ፣ ከያዕቆብና ከዮሐንስ ጋር፣ ከሰማይ መጡ እና የመልከ ጼዴቅ ክህነትን እና የዚህን ቁልፎች ለጆሴፍ ስሚዝ እና ለኦሊቨር ካውደሪ ሰጡ (ት. እና ቃ. ፳፯፥፲፪–፲፫፤ ፻፳፰፥፳)።
መጀመሪያይቱ የጴጥሮስ መልእክት
የመጀመሪያው መልእክት ከባቢሎን (ምናልባት ሮሜ) የተጻፈ ነበር እናም አሁን እስያ ታናሽ ተብሎ ለሚታወቀው ቦታ ኒሮ ክርስቲያኖችን ማሳደድ ከጀመረ ከቅርብ ጊዜ በኋላ ነበር የተላከው።
ምዕራፍ ፩ ስለክርስቶስ እንደ ቤዛ አስቀድሞ መቀባት ይናገራል። ምዕራፍ ፪–፫ ክርስቶስ የቤተክርስቲያኗ ዋና የማዕዘን ድንጋይ እንደሆነ፣ ቅዱሳን ልዑል ክህነትን እንደያዙ፣ እና ክርስቶስ በነፍስ እስር ቤት ውስጥ እንደሰበከ ይገልጻሉ። ምዕራፍ ፬–፭ ወንጌሉ ለምን ለሙታን እንደሚሰበክ እና ለምን ሽማግሌዎች መንጋዎችን መመገብ እንዳለባቸው ይገልጻሉ።
ሁለተኛይቱ የጴጥሮስ መልእክት
ምዕራፍ ፩ ቅዱሳንን ጥሪአቸውን እና ምርጫቸውን እንዲያረጋግጡ ይለምናል። ምዕራፍ ፪ ስለሀሰት አስተማሪዎች ያስጠነቅቃል። ምዕራፍ ፫ ስለኋለኛው ቀናት እና ስለክርስቶስ ዳግም ምፅዓት ይናገራል።