ክፍል ፻፲፫
በመጋቢት ፲፰፻፴፰ (እ.አ.አ.)፣ በፋር ዌስት፣ ምዙሪ ወይም አካባቢ ስለ ኢሳይያስ ፅሁፎች አንዳንድ መልሶች በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የተሰጠበት።
፩–፮፣ የእሴይ ግንድ፣ ከዚያም የሚመጣው በትር፣ እና የእሴይ ስርም ምን እንደሆኑ ተገልጸዋል፤ ፯–፲፣ በፅዮን የተበተኑት ቅሪቶች ለክህነት ስልጣን መብት አላቸው እና ወደ ጌታ እንዲመለሱም ተጠርተዋል።
፩ በኢሳይያስ ፲፩ኛ ምእራፍ በ፩ኛ፣ ፪ኛ፣ ፫ኛ፣ ፬ኝ፣ እና ፭ኛ አንቀጾች ውስጥ የተነገረለት ሀየእሴይ ግንድ ማን ነው?
፪ በእውነት ጌታ እንዲህ ይላል፥ ይህም ክርስቶስ ነው።
፫ በኢሳይያስ ፲፩ኛ ምእራፍ በአንደኛው አንቀፅ ውስጥ ከእሴይ ግንድ እንደሚመጣ የተነገረለት በትር ምንድን ነው?
፬ እነሆ፣ ጌታ እንዲህ ይላል፥ ይህም በከፊል የእሴይ ተወላጅ እና ሀየኤፍሬም ወይም የዮሴፍ ቤት አባል የሆነው፣ በእርሱም ላይ ብዙ ለሀይል ያረፈበት የክርስቶስ እጆች አገልጋይ የሆነው ነው።
፭ በኢሳይያስ ፲፩ኛ ምእራፍ ፲ኛ አንቀፅ ውስጥ የተነገረለት የእሴይ ስር ምንድን ነው?
፮ እነሆ፣ ጌታ እንዲህ ይላል፣ ይህም ሀለምልክት እና በመጨረሻዎቹ ቀናትም ህዝቤን ለለመሰብሰብ፣ ክህነትና የመንግስት ሐቁልፎች በመብት የእርሱ የሆነው የእሴይ፣ እንዲሁም የዮሴፍ ዘር ነው።
፯ የኢላየስ ሂግቢ ጥያቄዎች፥ በኢሳይያስ ፶፪ኛ ምእራፍ ፩ኛ አንቀጽ ውስጥ ፅዮን ሆይ፣ ኃይልሽን ልበሺ የሚለው ትእዛዝ ምን ማለቱ ነው—እና ኢሳይያስስ የሚያመለክተው የትኞቹን ህዝቦች ነው?
፰ የሚጠቁመውም እግዚአብሔር በመጨረሻዎቹ ቀናት ስለሚጠራቸው፣ ሀፅዮንን ዳግም ለማምጣትና እስራኤልን ለማዳን ክህነት መያዝ ስላለባቸው ስለእነርሱ ነው፤ እና ለኃይሏን መልበሷም ፅዮን በዘር ሐመብት ያላትን የክህነት ባለስልጣንነትን መልበሷ ሲሆን፤ ደግሞም ወደአጣችው ሀይል መመለሷ ነው።
፱ ፅዮን ከአንገት እስራት ስለመፈታቷ ምን እንረዳላን፤ ፪ኛው አንቀፅ?
፲ መረዳት ያለብን የቀሩት ሀተባእቶች ከወደቁበት ወደ ጌታ ለእንዲመለሱ በጥብቅ እንዲበረታቱ ነው፤ ይህንም ካደረጉ፣ የጌታ ቃል ኪዳንም እንደሚናገራቸው፣ ወይም ራዕይን እንደሚሰጣቸው ነው። ፮ኛ፣ ፯ኛ፣ እና ፰ኛ አንቀፅን ተመልከቱ። የአንገቷም እስራት ያለባት የእግዚአብሔር እርግማን፣ ወይም በአህዛብ መካከል የእስራኤል ቅሪቶች በመበተናቸው የደረሰባቸው ጉዳት ነው።