ክፍል ፸፯
በመጋቢት ፲፰፻፴፪ (እ.አ.አ.) አካባቢ ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የተሰጠ ራዕይ። የጆሴፍ ስሚዝ ታሪክ እንደሚገልጸው፣ “ቅዱሳን መጻህፍትን ከመተርጎም ጋር በተገናኘ፣ ስለቅዱስ ዮሐንስ ራዕይ የሚቀጥለውን መግለጫ ተቀበልኩ”።
፩–፬፣ አራዊት መንፈስ አላቸው እናም በዘለአለማዊ ደስታ ይኖራሉ፤ ፭–፯፣ ይህች ምድር የ፯ ሺህ አመታት ጊዜያዊ ህይወት አላት፤ ፰–፲፣ የተለያዩ መላእክት ወንጌልን ደግመው መለሱ እና በምድርም አገለገሉ፤ ፲፩፣ ፻፵፬ ሺህዎቹ መታተም ፲፪–፲፬፣ ክርስቶስ በሰባት ሺህ አመታት መጀመሪያ ውስጥ ይመጣል፤ ፲፭፣ ሁለት ነቢያት በአይሁድ ሀገሮች ይነሳሉ።
፩ ጥ. በራዕይ ምዕራፍ ፬፣ እና ቁጥር ፮ ውስጥ በዮሐንስ የተነገረው የብርጭቆ ሀባሕር ምንድን ነው?መ. ይህም ለምድር በተቀደሰ፣ በማይጠፋ፣ እና ሐዘለአለማዊ ሁኔታዋ ነው።
፪ ጥ. በዚህ ተመሳሳይ አንቀፅ ውስጥ ስለተነገሩት አራቱ እንስሳት ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. እነዚህ ገላጩ ዮሐንስ፣ ሀሰማይን፣ የእግዚአብሔርን ለገነትን፣ የሰውን፣ እናም የእንስሣትን፣ እና በምድርም የሚንቀሳቀሱት፣ እና የሰማይ አዕዋፋት ሐደስታን፤ መንፈሳዊ ነገሩ ጊዜአዊ በሆነው ምስል መሆኑን፤ እናም ጊዜአዊ ነገሩም መንፈሳዊ በሆነው መየተመሰለ መሆኑን፤ ሠየእንስሳ እና እግዚአብሔር የፈጠራቸው ሌሎች ፍጡራንም ደግመው የሰው ረመንፈስ በሰውየው ምስል እንደሆነ ለማሳየት የተጠቀመባቸው ምሳሌያዊ መግለጫዎች ናቸው።
፫ ጥ. አራቱ እንስሳት በልዩ እንስሣት የተወሰኑ ናቸው፣ ወይስ ክፍሎችን እና ስርዓቶችን የሚወክሉ ናቸው?መ. ለዮሐንስ ህያዋን ፍጡራን በየክፍሎቻቸው በተወሰነ ምድባዊ ስርዓታቸው ወይም በፍጥረት ሀተፅዕኖ አካባቢያቸው ውስጥ ክብራቸውን በመወከል፣ በዘለአለማዊ ለደስታቸው ሲደሰቱ፣ የታዩት፣ በአራት ልዩ እንስሳት የተወሰኑ ናቸው።
፬ ጥ. እንስሣቱ በነበራቸው አይኖች እና ክንፎች ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. አይኖቻቸው ብርሀን እና ሀእውቀትን እና በእውቀት የተሞሉ መሆናቸውን የሚወክሉ ናቸው፤ እናም ክንፎቻቸውም የመነቃነቅ፣ የመስራት፣ እናም ሌሎች ለሀይላትን የሚወክሉ ናቸው።
፭ ጥ. በዮሐንስ ስለተነገሩት ሀያ አራት ሀሽማግሌዎች ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. ዮሐንስ ያያቸው ሽማግሌዎች፣ በአገልግሎት ስራ ለታማኝ የነበሩ እና ሞተው የነበሩት ሽማግሌዎች እንደሆኑ፣ ሐበሰባቱ አብያተክርስቲያናት አባል የሆኑ፣ እና በእግዚአብሔር ገነት በሰማይ እንደሚገኙ ሊገባን ያስፈልገናል።
፮ ጥ. ዮሐንስ ስላየው፣ ከጀርባው በሰባት ሀማኅተም የተዘጋ መጽሐፍ ምን እንዲገባን ያስፈልገናል?መ. ይህም የተገለጠውን የእግዚአብሔር ፈቃድ፣ ለሚስጥራት፣ እና ስራዎች፤ በሰባት ሺ አመታት ኑሮ፣ ወይም ጊዜአዊ ህይወት፣ ጊዜ የተደበቁትን የዚህን ሐምድር አስተዳደር በሚመለከት እንደያዘ ሊገባን ያስፈልጋል።
፯ ጥ. ስለታተሙት ሰባት ማኅተሞች ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. የመጀመሪያው ማኅተም ሀየመጀመሪያውን ሺህ አመታት ነገሮችን እንደያዘ፣ እናም ሁለተኛውም ደግሞ የሁለተኛውን ሺ አመታት፣ እናም እስከሰባተኛው እንዲሁ እንደሚቀጥል ሊገባን ያስፈልጋል።
፰ ጥ. በራዕይ ፯ኛ ምዕራፍ እና ፩ኛ ቁጥር ውስጥ ስለተነገሩት አራት መላዕክት ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. እነዚህ መላዕክት ከእግዚአብሔር እንደተላኩ፣ ለእነርሱም፣ ህይወትን ለማዳን እናም ለማጥፋት፣ በምድር አራት ክፍሎች ላይ ሀይል እንደተሰጣቸው፤ እነዚህም ሀዘለአለማዊውን ወንጌል ለእያንዳንዱ ሕዝብ፣ ነገድ፣ ቋንቋ፣ እና ወገን በአደራ የሚሰጡ መሆኑን፤ ሰማያትን ለመዝጋት፣ በህይወትም ለማተም፣ ወይም የጭለማ ለአካባቢዎችንም ለመጣል ሀይል እንዳላቸው እንዲገባን ያስፈልጋል።
፱ ጥ. በራዕይ ፯ኛ ምዕራፍ እና ፪ኛ ቁጥር፣ ከምስራቅ ስለሚነሳው መልአክ ምን እንዲገባን ያስፈልገናል?መ. ከምስራቅ የሚነሳው መልአክ ሀበእስራኤል አስራ ሁለቱ ጎሳ ላይ የህያው እግዚአብሔር ማተሚያ የተሰጠው እንደሆነ እዲገባን ያስፈልጋል፤ ስለዚህ፣ ዘለአለማዊ ወንጌሉን ይዞ፣ የአምላካችንን ባሪያዎች ለግምባራቸውን እስክናትማቸው ድረስ ምድርን ቢሆን ወይም ባሕርን ወይም ዛፎችን አትጕዱ፣ ብሎ ወደ አራቱ መላእክት ይጮሀል። እናም፣ ከተቀበላችሁትም፣ ይህም የእስራኤልን ነገዶች ለመሰብሰብ እና ሁሉንም ነገሮች ሐደግሞ ለመመለስ የሚመጣው መኤልያስ ነበር።
፲ ጥ. በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የተጠቀሱት ነገሮች የሚከናወኑበት በምን ጊዜ ነው?መ. የሚከናወኑት ሀበስድስት ሺህ አመታት ውስጥ፣ ወይም በስድስተኛው ማኅተም በሚከፈትበት ነው።
፲፩ ጥ. ከእስራኤል ጎሳዎች ሁሉ መካከል፣ ሀየአንድ መቶ አርባ አራት ሺዎቹ መታተም—ከእያንዳንዱ ጎሳ አስራ ሁለት ሺ—ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. የታተሙት ዘለአለማዊውን ወንጌል እንዲያስተዳድሩ በእግዚአብሔር ቅዱሱ ስርዓት የተሾሙት ለሊቀ ካህናት እንደሆኑ እንዲገባን ያስፈልጋል፤ እነዚህም ወደ ሐበኩር ቤተክርስቲያን የመምጣት ፈቃድ ያሏቸውን እንዲያመጡ በምድር አገሮች ላይ ሀይል በተሰጣቸው መላዕክት ከእያንዳንዱ ሕዝብ፣ ነገድ፣ ቋንቋ፣ እና ወገን መካከል የተሾሙት ናቸውና።
፲፪ ጥ. በራዕይ ምእራፍ ፰ ውስጥ ስለተጠቀሰው ሀየመለከት መነፋት ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. እግዚአብሔር አለምን በስድስት ቀናት እንደሰራ፣ እና በሰባተኛው ቀን ስራውን እንደጨረሰ፣ እናም ለእንዲቀደስም እንዳደረገው፣ እናም ደግሞም በሰባተኛው ቀን ሰውን ከምድር ሐአፈር እንዳበጀው፣ እንዲሁም፣ በሰባት ሺ አመታት መጀመሪያ ላይ ጌታ አምላክ ምድርን መእንደሚቀድስ፣ እናም የሰውን ደህንነት እንደሚፈፅም፣ እናም ሁሉንም ነገሮች ሠእንደሚፈርድ፣ እናም ሁሉንም ነገሮች፣ በሁሉም ነገሮች መጨረሻ፣ ሲያትም በሀይሉ ካልጨመራቸው በስተቀር፣ ሁሉንም ነገሮች ረእንደሚያድን እንዲገባን ያስፈልጋል፤ እናም፣ በሰባተኛው ሺ አመታት መጀመሪያ፣ የሰባቱ መላዕክት መለከት ድምፅ የስራው መዘጋጃ እና መጨረሻ—ዳግሞ ከመምጣቱ በፊት መንገዱ የሚዘጋጅበት ነው።
፲፫ ጥ. በራዕይ ምዕራፍ ፱ ውስጥ የተጻፉት ነገሮች የሚከናወኑበት መቼ ነው?መ. እነዚህ የሚከናወኑት ሰባተኛው ማኅተም ከተከፈተ፣ ከክርስቶስ መመለስ በፊት ነው።
፲፬ ጥ. በራዕይ ምዕራፍ ፲ ውስጥ እንደተጠቀሰው፣ ዮሐንስ ሀስለበላት ታናሽ መጽሐፍ ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. ይህም የእስራኤልን ነገዶች ለለመሰብሰብ የተሰጠው ተልዕኮ፣ እናም ስርዓት እንደሆነ እንዲገባን ያስፈልጋል፤ እነሆ፣ እንደተጻፈው፣ ይህ መጥቶ ሁሉንም ነገሮች ሐዳግሞ መመለስ ያለበት ኤልያስ ነው።
፲፭ ጥ. በራዕይ ምዕራፍ አስራ አንድ ውስጥ ስለተጠቀሱት ሁለቱ ሀምስክሮች ምን ሊገባን ያስፈልገናል?መ. እነዚህም ለበመጨረሻው ቀናት፣ ሐበዳግም መመለሱ ጊዜ፣ እና ከተሰበሰቡ እና የኢየሩሳሌም ከተማን በአባቶቻቸው መምድር ላይ ለሚሰሩ ለአይሁዶች እንዲተነቢዩ ሠበአይሁድ ሀገሮች የሚነሱት ሁለት ነቢያት ናቸው።